እንደ ሀገር ለተመዘገቡ የልማትና ዲሞክራሲ ግንባታ ስኬቶች፣ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ሚና ከፍተኛ ነው – ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

(ሐምሌ 25/2017 ዓ.ም) በተጠናቀቀዉ በጀት ዓመት እንደ ሀገር የተመዘገቡ በርካታ የልማትና ዴሞክራሲ ግንባታ ስኬቶች፣ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሚና ከፍተኛ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አመራርና ሠራተኞች የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዕቅድን በአዳማ ከተማ እየገመገሙ ነው። የተቋሙ የዘንድሮ አፈጻጸም ከባለፈዉ ዓመት ጋር ሲነጻጸር ዉጤታማ የኮሙኒኬሽን ሥራዎች…

የፕሬስ መግለጫ

ኢትዮጵያዊነት ብያኔዉ የተሻለ ዓልሞ የላቀ ማሳካት ነው! ኢትዮጵያ የቀደምት ሥልጣኔ መነሻ፣ የጥቍር ሕዝቦች የነፃነት ቀንዲል ብቻ አይደለችም፤ ኢትዮጵያ የመጪዉ ትውልድ የተስፋ ምድር ጭምር ናት፡፡ ኢትዮጵያውያን ደግሞ በጋራ ሉዓላዊነትን ከማስከበር ባሻገር የሚገለጹ፣ የመቻል ተምሳሌቶች ናቸው፡፡ “በጋራ እንችላለን” ብለው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን እውን አደረጉ፡፡ “በጋራ ኢትዮጵያን አረንጓዴ እናልብስ” ብለው ላለፉት ስድስት ዓመታት ከ40 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን…

አረንጓዴ አሻራ ለኢትዮጵያ አዲስ ምዕራፍ እየከፈተ ነዉ _ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

(ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም) አረንጓዴ አሻራ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ እየከፈተ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አመራርና አጠቃላይ ሰራተኞች በአንድ ጀምበር 700 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሃ ግብር ዘነበወርቅ የሚገኘዉ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ግቢ አረንጓዴ አሻራቸውን አስቀምጧል፡፡ በኢቢሲ ግቢ በተከናወነው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር በርካታ የቡና ችግኞች ተተክለዋል፡፡…

የፕሬስ መግለጫ

ጉባኤዉ ኢትዮጵያ ልምድ ያካፈለችበት እና የመፍትሔ አካል ኾና የቀረበችበት ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ያስተናገደችዉ 2ኛዉ የዓለም የምግብ ሥርዐት ጉባኤ ልምድ ያካፈለችበት እና ለምግብ ሥርዐት መስተካከል መፍትሔዎችን ያቀረበችበት ነበር፡፡ የኢትዮጵያ እና የጣሊያን መንግሥታት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በመቀናጀት ያዘጋጁት የዓለም የምግብ ሥርዐት ጉባኤ በርካታ መሪዎች፣ የግብርናዉ ዘርፍ ተመራማሪ ግለሰቦች እና ተቋማት እንዲሁም ሌሎች የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በታደሙበት በአዲስ…

 “ኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት ሽግግርን እዉን ለማድረግ ስኬታማ ስራዎችን አከናዉናለች” – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

 “ኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት ሽግግርን እዉን ለማድረግ ስኬታማ ስራዎችን አከናዉናለች” – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ያለዉ 2ኛው የተባበሩት መንግስታት የምግብ ስርዓት ጉባኤ (UNFSS+4) ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት ሽግግርን እዉን ለማድረግ ስኬታማ ስራዎችን ስታከናዉን መቆየቷን ገልጸዋል፡፡ በመላው አፍሪካ የምግብ ሥርዓትን ለመለወጥ እየተሰሩ ያሉ አኩሪ ስራዎችንም አድንቀዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዓለም አቀፍ መሪዎች፣ የልማት አጋሮች እና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በተገኙበት ባደረጉት ንግግር፣ ረሃብን፣…

የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እየሠራን የዓለም የምግብ ሥርዐት ጉባኤን ለማስተናገድ ተዘጋጅተናል!

ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በጀመረቻቸዉ ጥረቶች በርካታ ስኬቶች ተመዝግበዋል፤ ለላቀ ስኬትም ጥረቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ በዚህ ወሳኝ ወቅት ኢትዮጵያ ከጣልያን መንግሥት እና ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በመቀናጀት 2ኛዉን የዓለም የምግብ ሥርዐት ጉባኤ እንድታዘጋጅ ተመርጣለች፡፡ ይህም በኹለትዮሽ እና ባለብዙ ወገን ግንኙነቶች ውስጥ ኢትዮጵያ እየተጫወተች ያለዉን ሚና የሚጎላ፣ በሥርዐተ ምግብ ዙሪያ የጀመረቻቸዉን ስኬታማ ተግባራት የሚያበረታታ ነው፡፡ ከዐራት ዓመታት…

በአንድ ጀምበር ሚሊዮኖችን በመትከል የማንሰራራት ታሪካዊ ጉዞ አካል እንሁን!

ኢትዮጵያን ወደ ነበራት ጥንታዊ የደን ሽፋን በመመለስ አረንጓዴ ካባ ለማልበስ የጀመርነው ጥረት 7ኛ ዓመቱ ላይ ደርሷል፤ 7ኛ ዓመት የጥረታችንን ጅማሮ የምንዘክረዉ ደግሞ በአንድ ጀምበር 700 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ነው፡፡ ባለፉት 6 ዓመታት የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዟችን ኢትዮጵያውያን ከሁሉም አቅጣጫ፣ ከደጋ እስከ ቆላ በጋራ ባደረግነዉ ጥረት 40 ቢሊዮን ችግኞች በላይ ተክለናል፤ የኢትዮጵያን የደን ሽፋንም እስከ ባለፈዉ ዓመት…

ሀገራዊ የልማት እቅዱ የተገኙ እምርታዊ ዉጤቶችን የሚያስቀጥልና የተደመረ አቅምን የሚፈጥር ነዉ- ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

ሀገራዊ የልማት እቅዱ የተገኙ እምርታዊ ዉጤቶችን የሚያስቀጥልና የተደመረ አቅምን የሚፈጥር ነዉ- ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

የ2018 ሀገራዊ የልማት አቅድ በሁሉም ዘርፎች የተገኙ እምርታዊ ዉጤቶችን የሚያስቀጥልና ለላቀ ዉጤት የተደመረ አቅም የሚፈጥር እቅድ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የአገልግሎቱ አመራርና ሰራተኞችም በእቅዱ ላይ ዛሬ ዉይይት አድርገዋል፡፡ የኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ሀገራዊ እቅዱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ፣ ኢትዮጵያ በ2017 ዓ.ም በሁሉም ዘርፎች ያስመዘገበችዉ የኢኮኖሚ እድገት እምርታ የታየበት መሆኑን…

አረንጓዴ ዐሻራ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተያዘዉን ግብ እዉን የሚያደርግ ነዉ

አረንጓዴ ዐሻራ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተያዘዉን ግብ እዉን የሚያደርግ ነዉ

የአረንጓዴ ዐሻራ መረሃ ግብር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተያዘዉን ግብ እዉን የሚያደርግ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽ አገልግሎት ገለጸ፡፡ መረሃ ግብሩ የውሃ ሀብትንና የብዝሃ ህይወት ጥበቃን በማረጋገጥ ረገድም  ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት፣ የቤተ መንግሥት አስተዳደር እና የኮሙኒኬሽን ባለሥልጣን አመራርና ሠራተኞች፣ የብልፅግና ፓርቲ  ህብረት አባላት በጋራ ትናንት ሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም በመልካሳ ቤተመንግሥት የችግኝ…

መገናኛ ብዙሃን የተመድ የሥርዓተ ምግብ ጉባኤን ሀገራዊ ፋይዳ በመገንዘብ የተደራጀ መረጃ ተደራሽ ሊያደርጉ ይገባል – የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

መገናኛ ብዙሃን የተመድ የሥርዓተ ምግብ ጉባኤን ሀገራዊ ፋይዳ በመገንዘብ የተደራጀ መረጃ ተደራሽ ሊያደርጉ ይገባል – የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን ኢትዮጵያ የምታስተናግደውን የተመድ የሥርዓተ ምግብ ጉባኤ ሀገራዊ ፋይዳ በመገንዘብ የተደራጀ መረጃ ተደራሽ ሊያደርጉ እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ። ኢትዮጵያ 2ኛውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሥርዓተ-ምግብ ጉባኤን ከሁለት ሳምንት በኋላ ታስተናግዳለች። የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት መገናኛ ብዙሃን ጉባኤውን በተመለከተ ሊኖራቸው የሚገባው ግንዛቤ እና የሥርዓተ ምግብ ሽግግር ፅንሰ…