የፖሊሲ ጉዳይ ቅኝት – ሐምሌ 3፣ 2018 ዓ.ም
#PMOEthiopia
#PMOEthiopia
በመጀመሪያ ደረጃ የሚያስፈልገን ሰላም፣ ትብብር እና አብሮ መስራት ነው። በትግራይ ክልል ዳግም ጦርነት እንዲቀሰቀስ ከፍተኛ ፍላጎት ያላቸው አካላት ቢኖሩም፤ ጦርነት አውዳሚና ትርፍ የለሽ በመሆኑ እምቢ ብለናል። አሁንም ቢሆን ለሰላም፣ ለንግግርና ለውይይት በራችን ምንጊዜም ክፍት ነው። የራሳችንን ጥቅም መስዋዕት አድርገንና ተጎድተን እንኳ በትግራይ ዘላቂ ሰላም የሚመጣ ከሆነ ዋነኛ ፍላጎታችን እርሱ ብቻ ነው። እርስ በርስ መጠላለፍና መውደቅ…
የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የግንባታ ሂደት – ከሰኔ 26/2015 ዓ.ም ➤ ሰኔ 27/2018 ዓ.ም. #PMOEthiopia#VisitEthiopia#EthiopiaDelivers
የውጭ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት እና የሥራ ዕድልን በመፍጠር፣ ዘርፉ ለሌሎች ኢንዱስትሪዎችም የማይናወጥ መሠረት ሆኗል። ይኸው ወሳኝ እመርታ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር አማካኝነት በሀገር በቀል መፍትሔዎች የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት መለወጥና የሀገርን ኢኮኖሚ ማሳደግ እንደሚቻል በተግባር እያሳየን ነው። በጋራ እናልማ፣ እናምርት፣ እንበልጽግ! #EthiopiaDelivers #PMOEthiopia
“የሩሲያ ፌዴሬሽን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር ሰርጌ ላቭሮቭ እና የልዑክ ቡድናቸው ጋር ተወያይተናል። ማምሻውን በነበረን የጋራ ጊዜ፣ የሁለትዮሽ ግንኙነቶች እና አዳዲስ የትብብር ዕድሎች ዙሪያ የተቃኘ ውይይት አድርገናል።”
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 30ኛው መደበኛ ስብሰባ ላይ በሰላምና ደህንነት፣ ኢኮኖሚ፣ ጤና፣ ትምህርት፣ የውጭ ግንኙነትን ጨምሮ በሌሎች ዘርፎች ዙሪያ የመንግሥትን አፈጻጸም እና የቀጣይ እቅዶች አብራርተዋል። የፕሪቶሪያው ስምምነት ጦርነቱን ለማቆም የተደረገ መሆኑን ጠቅሰው፣ በአሁኑ ወቅት በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርና በክልሉ የሚታዩ አዳዲስ ውጥረቶችን እንዲሁም የክልሉን ሰላም ለማደናቀፍ የሚደረጉ…
በአፍሪካ በስልጣን ላይ ያለ መንግስት ህገ መንግሥት አሻሽሎ የሥልጣን ዘመን ሲጨምር እንጂ ሲገደብ ታይቶ አይታወቅም:: በሀገራዊ ምክክሩ ብልጽግና አጀንዳዬ ብሎ ካቀረበው ጉዳይ አንዱ የመንግሥት የሥልጣን ጊዜ እንዲገደብ የሚጠይቅበት ነው:: ይህ ለልጆቻችን መሠረት የሚጥል ልምምድ ነው!
የCOP32 ኢትዮጵያን ይፋዊ የድህረ-ገጽና ማኅበራዊ ትስስር ገጾች በመከታተል ትክክለኛ፣ የተረጋገጠና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ። በተመሳሳይ ስያሜዎች ሀሰተኛ ገጾች የተከፈቱ ሲሆን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ብቸኛ ይፋዊ የCOP32 ኢትዮጵያ ገጾችን በመከታተል፤ ከሀሰተኛ ገጾች እንዲጠነቀቁ እናሳስባለን። ኢትዮጵያ ይህን ዓለም-አቀፋዊ የአየር ንብረት ጉባዔ ለማዘጋጀት የምታደርገው ጉዞ አካል ይሁኑ! አማርኛ፡ •ፊስቡክ አማርኛ: https://web.facebook.com/cop32ethiopiaamharic/ •ቴሌግራም: https://t.me/cop32ethiopia እንግሊዘኛ፡ •ድህረ ገጽ: https://cop32ethiopia.et/ •ሳብስታክ: https://substack.com/@cop32ethiopia?utm_source=share……
