መገናኛ ብዙሃን የተመድ የሥርዓተ ምግብ ጉባኤን ሀገራዊ ፋይዳ በመገንዘብ የተደራጀ መረጃ ተደራሽ ሊያደርጉ ይገባል – የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን ኢትዮጵያ የምታስተናግደውን የተመድ የሥርዓተ ምግብ ጉባኤ ሀገራዊ ፋይዳ በመገንዘብ የተደራጀ መረጃ ተደራሽ ሊያደርጉ እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ። ኢትዮጵያ 2ኛውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሥርዓተ-ምግብ ጉባኤን ከሁለት ሳምንት በኋላ ታስተናግዳለች። የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት መገናኛ ብዙሃን ጉባኤውን በተመለከተ ሊኖራቸው የሚገባው ግንዛቤ እና የሥርዓተ ምግብ ሽግግር ፅንሰ…