




የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን እና የኢትዮጵያዊያንን ዉበት የሚያጎላ ነው፡፡
ኢትዮጵያ የብዝኃ ቋንቋ፣ ብዝኃ ባህልና ብዝኃ ማንነት ሃገር ናት፡፡ ብዝኃነት ለኢትዮጵያዊያን ተፈጥሯችን፣ ዉበታችንና የጥንካሬአችን ምንጭ ነው፡፡ ብዝኃ ማንነት ያለበት ሕዝቦች ሀገር መሆናችን ጸጋችን ነው፤ ብዝኃነት የኢትዮጵያ ተጨባጭ እዉነታና ውብትም ነው፡፡ በኢትዮጵያ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ሂደት አንድ ጠንካራ ሀገር ለመገንባት በርካታ መንገዶች ተሞክሯል፡፡ ነባሩንና ተፈጥሯችን የሆነውን ብዝኃ ማንነትን በአንድ ወጥ ማንነት ለመቀየር ብዙ ተለፍቶበታል፡፡ በፖሊሲና ተቋማዊ አሰራር…

ክቡር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ
ክቡር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ከህዳር 25/2017 ዓ.ም ጀምረው የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው እንዲያገለግሉ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተሹመዋል። ሚኒስትር ዴኤታው በዛሬው ዕለት በአገልግሎቱ አመራሮችና ሠራተኞች የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል ተደርጎላቸው ሥራቸውን ጀምረዋል። መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንልዎ ተመኝተናል!!


የኮሙኒኬሽን ተቋማት በወቅታዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የተናበበና የተቀናጀ የመረጃ ተደራሽነትን ይበልጥ ማጠናከር እንዳለባቸው ተገለፀ
በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የተናበበና የተቀናጀ መረጃ ከተቋማት ጋር የመለዋወጥ ዐቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ መሻሻል እያመጣ እና ውጤት እየተመዘገበ መሆኑንና ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎቱ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ አስታውቀዋል። የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የፌዴራል እና የተጠሪ ተቋማት የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራዎች የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ የጋራ መድረክ በአዳማ እየተካሄደ ነው።…

19ኛው የብሔር፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በተቋም ደረጃ በድምቀት ተከበረ ፡፡
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2017(የኢፌዴሪ መ.ኮ.አ) “ሀገራዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት “በሚል መሪ ቃል 19ኛው የብሔር፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በኢፌዴሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በዛሬው ዕለት ተከብሯል ። በመርሐ ግብሩ የአገልግሎቱ ሚኒስትር ክቡር ዶክተር ለገሠ ቱሉን ጨምሮ ክቡር ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ እና የጽህፈት ቤት ኃላፊው አቶ ዝናቡ ቱኑ ተገኝተዋል ። በዓሉ በተለያዩ ሁነቶች የተከበረ ሲሆን…
