የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር

የክቡር ሚኒስትሩ መልክት

ኮሙኒኬሽን በባህሪው መረጃን አውጥቶ መናገር፣ ስሜትን፣ ፍላጎትን፣ ሃሳብንና አመለካከትን በቃላት፣ በምስል ወይም በጽሁፍ መልክ ለሌላው መግለፅ የሌላውንም ሃሳብ መቀበል፣ አብሮነትን ፈጥሮ መጎዳኘት  ”በእኛነት” መንፈስ የሚነገር  ”እኛ” የሚል ሀሳብ የሚቀርብበት የተግባቦት ስርዓት ነው፡፡ ባለንበት የሉዓላዊነት፣ የመረጃና የባህል ዘመን ኮሙኒኬሽን ይበልጥ ተፈላጊ ነዉ። ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣው የአለም ሚዲያን በብቸኝነት ከመቆጣጠር እስከ ሰብዓዊ መብት ጉዳዮች፣ የጤናና የግብርና ልማት ዘመቻዎች፣ የንግግር ነጻነት እስከ የህብረተሰብ አንጋቢገቢ ጉዳዮች ድረስ ኮሙኒኬሽን እጅግ ተፈላጊ እንዲሆን አድርገዉታል፡፡

       በታሪክ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ ረጅም ርቀት የተጓዘው የዛሬዉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ተልእኮ ቀልጣፋና ዉጤታማ መረጃና የተግባቦት ሥርዓት በመዘርጋት የኢትዮጵያ መንግስት አጀንዳዎች የተሻለ ተቀባይነትና ተፈፃሚነት እንዲኖራቸው ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃን በማቅረብ፣ ህዝቡ በዋና ዋና  ሀገራዊ ጉዳዮች መግባባት እንዲፈጥርና የሀገሪቱ መልካም ገጽታና ተሰሚነት እንዲጎለብት ስትራቴጂካዊ አመራር መስጠት ነዉ፡፡ የተቋሙ የተግባቦት ስራ ዘመነ ግሎባላይዜሽን የደረሰበትን የዲጂታል ሚዲያን፣ ፈጣን የመረጃ ስርጭትና የነቃ ህብረተሰብን መረጃ ፍላጎት ጥማት ለማርካት ከየትኛዉም ወቅት ልቆና ቀልጥፎ በመገኘት የዘርፉን ስራ መምራትና መከወን ይጠበቅበታል፡፡ ዓለም አቀፋዊና ሀገራዊ ነባራዊና ተለዋዋጭ ሁኔታ ዉስጥ ሆኖ ህብረተሰቡ ከደረሰበት የአስተሳሰብ ከፍታ፣ የለዉጥና የእድገት ልህቀት ጋር የሚራመድ ተቋም መሆን ይጠበቅታል፡፡

    ተቋሙ ቁልፍ የመንግስት የመረጃ ምንጭነቱንና የብቁ ቃል አቀባይነት ሚናውን በአግባቡ መወጣት እንዲችል የተቀናጀና የተናበበ የመረጃ ፍሰት እንዲኖር ማድረግ፤ ብቁ ምላሽ ሰጪ፣ አሳታፊና ተደራሽ መሆን ይኖርበታል፡፡ ህገመንግስቱን መሰረት ባደረጉ አንኳር ጉዳዮች፤ በብሔራዊ ጥቅሞች፤ በሰላምና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ፤ የሀገሪቱን ገፅታ በመገንባት ረገድ ከሁሉም የሚዲያ አውታሮች ጋር በትብብርና በመደጋገፍ መስራትም ይጠበቅበታል፡፡

 

ይህንን ተልዕኮዉን ለመወጣት፣ የተቀናጀና ውጤታማ ስራ ለማከናወን እንዲቻል በብቁ ተቋማዊ አደራጃጀት፣ የሰዉ ሃይል፣ ቁሳቁስና አሰራር ራሱን መጠናከርና ማዘመን ይኖርበታል፡፡ ከሚዲያዎች ጋር በትብብርና መደጋገፍ አብሮ መስራትን፣ መረጃና ቴክኖሎጂ መጋራትን፣ የአቅም ክፍተቶችን በመለየት እዉቀትና ክህሎትን ለመገንባት መስራት ይገባናል፡፡

ይህ ድረገፅ ከላይ የተገለጹ አንኳር ጉዳዮችንና የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ተልዕኮዎችን በማሳካት በኩል ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡ ይህን ድረገፅ በመጠቀም የምናሰራጫቸዉን መረጃዎች በማጋራት፣ በመዉደድ እና ገንቢ አስተያያት በመጠስት መረጃዎችን ተደራሽ ለምታደርጉ ሁሉ ምስጋናችን ወደር የለዉም፡፡

አመሰግናለሁ!

ዉጤታማ ተግባቦት ለኢትዮጵያ ልዕልና!

ክቡር ሚኒስትር ዴኤታዎች

ክቡር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የሚዲያ ግንኙነት ክትትልና መረጃ ማደራጃ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ

ክቡር አቶ ከበደ ደሲሳ

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የህዝብ ግንኙነት እና ተቋማት ማስተባበርያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ