የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት!!
በሁለትዮሽ መድረካችን ወቅት ላደረግነው ጥልቅ ውይይት ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን አመሰግናለሁ። በሁለቱ ሀገሮቻችን ታሪካዊ ቁርኝት ላይ የተመሠረተው የሁለትዮሽ ግንኙነታችን እያደገ ቀጥሏል። ከዚህ በተጨማሪ የጋራችን የሆነው የብሪክስ መድረክ ሰፋ ላለ የኢኮኖሚ ትብብር እንድንሰራ በር ከፍቶልናል።

በሁለትዮሽ መድረካችን ወቅት ላደረግነው ጥልቅ ውይይት ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን አመሰግናለሁ። በሁለቱ ሀገሮቻችን ታሪካዊ ቁርኝት ላይ የተመሠረተው የሁለትዮሽ ግንኙነታችን እያደገ ቀጥሏል። ከዚህ በተጨማሪ የጋራችን የሆነው የብሪክስ መድረክ ሰፋ ላለ የኢኮኖሚ ትብብር እንድንሰራ በር ከፍቶልናል።

129ኛው የዓድዋ ድል በዓል በድምቀት ተከበረ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም ታሪካዊዉ የዘንድሮ የዓድዋ ድል በዓል፣ “ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል” በሚል መሪ ቃል የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀስላሴ፣ የመከላከያ ሚኒስትር ኢ/ር አይሻ መሐመድ እና የቀድሞው የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋኪ ማህማትን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፤ አርበኞች፣ የመከላከያና የፀጥታ አካላት አመራሮች፣ ዲፕሎማቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች…
• የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመት 8 ሚሊዮን ሰዉ ሲያጓጓዝ የነበረ ሲሆን፣ ባለፉት 6 ወራት 10.7 ሚሊዮን ሰዉ አጓጉዟል፡፡ በዚህ ዓመት በትንሹ ወደ 22 ሚሊዮን ለማድረስ እየተሰራ ነዉ፡፡ አየር መንገዱ በመጠን፣ በመዳረሻና በሚያጓጉዘዉ ሰዉ በእጅጉ ጨምሯል፡፡ • ሞባይልን በተመለከተ በለዉጡ ጊዜ 37 ሚሊዮን ዜጎች ሞባይልን ይጠቀሙ ነበር፡፡ ዘሬ ኢትዮ-ቴሌኮም ብቻ 87 ሚሊዮን ዜጎች፣ ሳፋሪኮም ደግሞ ከ10…
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ሁሉን አቀፍና አካታች የዲጂታል አገልግሎቶች የሚቀርቡበት፣ ዜጎችን ማዕከል ያደረገ ስርዓትን በመዘርጋት፣ ሉዓላዊና ደህንነቱ የተጠበቀ አውድን ለመፍጠር ቁልፍ ሚና ይኖረዋል። Post Views: 127
ዘመናዊ የግብርና አሠራሮች የኢትዮጵያን ግብርና በመለወጥ፣ አርሶ አደሮች ምርትን እንዲያሳድጉ፣ ቅልጥፍናን እንዲያሻሽሉ እና ከተለዋዋጭ ሁኔታዎች ጋር እንዲላመዱ እያገዛቸው ነው። ከተሻሻሉ ዘሮች ወደ ተሻለ መስኖ እና ቴክኖሎጂ፣ ፈጠራዎች በገጠሩ ማኅበረሰብ ውስጥ ያለውን ኑሮ እያጠናከሩ ይገኛሉ። ግብርና የሀገሪቱ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ሆኖ ቀጥሏል፣ ዕድገትን በማነሣሣት፣ ብልጽግናን በመደገፍ እና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ጉልሕ ሚና አሁንም…
የንግድ ሚዲያዎች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ማስከበርና ለትውልድ የሚሻገሩ ሀገራዊ የልማት ሥራዎችን አጀንዳ አድርጎ በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅባቸው የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። መንግስት በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከንግድ ሚዲያዎች ጋር ይበልጥ ተቀራርቦ እንደሚሰራ ገልጿል። መንግሥትና የንግድ ሚዲያዎች በሀገር ግንባታ ሥራዎች ላይ ይበልጥ ተቀራርበው መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ውይይት ዛሬ ተካሂዷል። በሀገራዊ ለውጥ ጉዞ የተገኙ ስኬቶችን ማሳወቅ፣ የገጠሙ…
“ዛሬ ያስጀመርነው የቡሳ ጎኖፋ ኦሮሚያ የተቀናጀ የምግብ ኢንዱስትሪ ግንባታ የበቆሎ እና ማሽላ ዱቄት እንዲሁም 14 ተጓዳኝ የበቆሎ ውጤት ምርቶችን ለማምረት የታቀደ ነው። ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ወደ ስራ ሲግባ በቀን 2000 ቶን በቆሎ እና 120 ቶን ማሽላ የማምረት አቅም ይኖረዋል። ከ6500 በላይ ለሚሆኑ ሠራተኞች ቋሚ እና ጊዜያዊ የሥራ እድል የሚፈጥር ሲሆን ለአካባቢው አርሶአደሮች፣ ለኅብረት ሥራ ማኅበራት እና…