ተቋማት ሲጠናከሩ ሀገር ትጸናለች፤ የዴሞክራሲ ሥርዓትም መሠረት ይይዛል!!

ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም ሀገራችን ኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግናን፣ ዘላቂ ሰላምን እና እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን እውን ለማድረግ ባለፉት ዓመታት ያከናወነቻቸው ጥልቅ ተቋማዊ ማሻሻያዎች እና ያስመዘገበቻቸው ተጨባጭ ውጤቶች መሠረት እየያዙና እየጸኑ መጥተዋል። ሀገር በጠንካራ ተቋማቶቿ ትገልጻለች፤ ለዚህም መንግሥት ለተቋማት መጠናከር በሰጠው ትኩረት ሀገራዊ ሉዓላዊነት በጽናት የሚያስከብሩ፣ የዴሞክራሲ ሥርዓትን የሚተክሉና የሕዝብን ውሳኔ ሰጪነት የሚያረጋግጡ ለትውልድ ተስፋ፣ ለቀጠናው ደግሞ አስተማማኝ…

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ የነቢዩ መሐመድ ታሪክ ትውልድን ለበጎ ከሚቀርጹ ታሪኮች መካከል አንዱ ነው፡፡ የተጠሩበትን ዓላማ ማክበር፤ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ መክፈል፤ የተጠሩበትን ለሌሎች ማካፈል፤ የተጠሩበትን አክብሮ መኖር – እነዚህ ሁሉ ሺ መጻሕፍት የሚወጧቸው ትምህርቶች ናቸው፡፡ ነቢዩ የተጠሩበትን ዓላማ በሚገባ ስለተገነዘቡ አክብረው ኖረዋል፡፡ የተጠሩት ለተራና ርካሽ ነገር እንዳልሆነ ተገንዝበዋል፡፡ የተጠሩት ትውልድን ለመቅረጽና ታሪክን…

“የሀገራዊ ምክክር ግቡ ጊዜያዊ የፖለቲካ መድህን ማግኘት ሳይሆን ለሀገር ዕድገት የሚበጅ ትጉህ እርምጃና ዘላቂ ፍኖትን መተለም ነው” – ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ

“የሀገራዊ ምክክር ግቡ ጊዜያዊ የፖለቲካ መድህን ማግኘት ሳይሆን ለሀገር ዕድገት የሚበጅ ትጉህ እርምጃና ዘላቂ ፍኖትን መተለም ነው” – ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ

ከኃይል አዙሪት ወደ ሐሳብ ልዕልና ታሪካዊ ምዕራፍ!

ነሐሴ 17/2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ የዘመናት የፖለቲካ ቁርሾዎቿን እና አውዳሚ የደም አዙሪትን በመስበር፣ በሀገራዊ ምክክር ሂደት አዲስ የዲሞክራሲ እና የሰላም ምዕራፍ መክፈቷ በትናንትናው ዕለት በታላቅ ብሔራዊ ኩራት ተበስሯል። ባለፉት 4 ዓመታት የዝግጅት ምዕራፍ ውስጥ አልፎ ከ4 ሺህ በላይ ወኪሎችን በማሳተፍ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለ46 ቀናት የተካሄደው ይህ ታሪካዊ ጉባኤ የሀገረ-መንግሥት ታሪካዊ ተቃርኖዎች በአፈሙዝ…

የገጠር ልማት መለካት ያለበት በሚገነቡት መሠረተ ልማቶች ብቻ ሳይሆን፣ ተከትሎ በሚመጣው የሰዎች ሕይወት ለውጥ መሆን አለበት።

‎‎በመሆኑም የገጠር ኮሪደር ልማት ውጥን ተግባራዊና ሰውን ማዕከል ያደረገ አካሄድን በመከተል ላይ ይገኛል። ይህም ትስስርን ማሻሻል፣ ምቹ የኑሮ ሁኔታዎችን መፍጠር እና በገጠር ማሕበረሰብ ውስጥ የኢኮኖሚ ዕድሎችን ማስፋፋት ነው። ‎‎የዚህ ዐበይት ግብ የተበታተነና የተቆራረጠ ሐብትን በማስተካከል አምራች፣ እርስ በርስ የተሳሰሩ፣ ዘላቂ ልማት ያላቸው እንዲሁም ለመኖርና ለመሥራት ማራኪ የሆኑ የገጠር አካባቢዎችን መገንባት ነው። #PMOEthiopia#EthiopiaDelivers