ዜናዎች

Screenshot 2026-03-03 092401
53ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች
የካቲት 23 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 53ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው መደመር የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በአዋጅ ቁጥር 1294/2015 መሠረት ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ የሚቋቋም ሲሆን በዘርፉ ወጣቶችን ለማሰልጠንና ለሀገር ግንባታ ወሳኝ የሆኑ ምሁራንን ለማፍራት የሚሰራ ነው፡፡ ደንቡ የዩኒቨርሲቲውን ተግባርና ሃላፊነት በመደንገግ ተቋሙ ለሀገር ዕድገት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ የህግ ማዕቀፍ ሆኖ እንዲያገለግል ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው ለባለሃብቶች ካሳ ለመክፈል ግዴታ የሚገባበትን ሁኔታ ለመወሰን በቀረበ ደንብ ላይ ነው፡፡ ባለሀብቶች የሀገራችንን የኢኮኖሚ እድገት ሊያፋጥኑ በሚችሉ ትላልቅ ፕሮጀክቶች እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንዲያስችል ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ 3. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው በሶስት የፋይናንስ ድጋፍ ሰምምነቶች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪው ለብሄራዊ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስፋፊያ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል ከኮሪያ ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ የስልሳ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሃያ ሶስት ሺ /60,223,000/ የአሜሪካን...