#ኢትዮጵያ_በዚህ_ሳምንት
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
ጳጉሜን 1 ቀን 2016 ዓ/ም በዛሬው ዕለት በመላው የሀገሪቱ አካባቢዎች “የመሻገር ቀን” በሚል ስያሜ በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ይውላል፡፡ ዕለቱ “የመሻገር ጥሪቶች፣ የአዲስ ብርሃን ወረቶች በሚል መሪ ቃል” ይከበራል፡፡ መሻገር ከአንዱ ወደ ሌላኛው የሕይወት ምዕራፍ ሽግግር የምናደርግበት ተፈጥሯዊ ሂደት ነው። አሮጌዉ ዘመን ተጠናቅቆ ወደ ዐዲሱ ዓመት የምንሸጋገርባት የጳጕሜን ወር የመጀመሪያው ዕለትን ስናከበር በተጠናቀቀዉ ዓመት ስኬቶችን ያስመዘገብንባቸው…
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያውያን ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን ተክለዋል፤ ይህ ንቅናቄ የደን ሽፋንን ከ17% ገደማ ወደ 23.6% ያሳደገ ሲሆን፣ 1.2 ሚሊዮን የሥራ እድሎችንም ፈጥሯል፣ ለበርካታ አስርት ዓመታት የነበረውን የመሬት መራቆት መቀልበስ ተችሏል! #PMOEthiopia#EthiopiaDelivers#GreenLegacy ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication Post Views: 31
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዎች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሳባ ላይ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በኢኮኖሚው ዘርፍ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ኢትዮጵያ የብዝሃ የኢኮኖሚ ፖሊሲ በመከተሏ ዘርፈ ብዙ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከዚህ ቀደም ግብርና መር የነበረው፣ አሁን ግብርናን ጨምሮ በማኑፋክቸሪንግ ፣በማዕድን፣ በቱሪዝም ፣በእንዱስትሪ እና በተክኖሎጂ…
ፕሬዚዳንቱ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክርቤቶች 4ኛ የሥራ ዘመን የጋራ ጉባኤ የመክፈቻ ንግግር ላይ እንዳሉት በበጀት ዓመቱ በኢኮኖሚ ዘርፍ ከሚደረጉት ጥረቶች በታክስ መረቡ ያልገቡትን ወደታክስ መረቡ በማስገባትና አዳዲስ የታክስ ምንጮችን በማካተት አጠቃላይ የመንግስትን ገቢ 1 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር ለማድረስ ይሰራል ብለዋል፡፡ ከታክስ የሚሰበሰበው ገቢ አጠቃላይ የሃገር ውስጥ ገቢ የሚኖረው ድርሻ 8 ነጥብ 3 በመቶ…
የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ የእዳ ጫና፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የገበያ አለመረጋጋት ከለውጡ በፊት የነበሩ የማክሮ ኢኮኖሚው ዋና ስብራቶች ሆነው ቆይተዋል።መንግሥት እነዚህን ስብራቶች ለመለወጥ በወሰዳቸው የለውጥ ተግባራት አሁን ላይ ውጤቶች እየተመዘገቡ ይገኛሉ። ይህም ለውጥ ኢትዮጵያ በአፍሪካ በፍጥነት እያደጉ ካሉ ሃገራት መካከል እንድትሆን አስችሏታል። የመጀመሪያው እና ሁለተኛው የሃገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ጠንካራ እና አዳዲስ ተቋማት እንዲፈጠሩ አስችሏል።…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚታየው የእሴት ሰንሰለት በበርካታ ሁኔታዎች የሚገለጽ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የዘርፉ እንቅስቃሴዎች ነገ ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ በእርግጠኝነት መተንበይ የማይቻልበት ዓለም አቀፋዊ ተጨባጭ ሁኔታ ተፈጥሯል። በተለይም የተለያዩ አገራት የራሳቸውን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበር ሲሉ በሌሎች ላይ ጉዳት የሚያደርሱ የንግድ ውጥረቶች እንዲፈጠሩ የሚያደርጉበት አጋጣሚ መኖሩን መገንዘብ ያስፈልጋል። ይህም በዓለም አቀፍ የንግድ…