ሃምሌ 10 በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኞች! ወቅታዊ መረጃ ከማለዳ 12 ሰአት እስከ 3:30
ሃምሌ 10 በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኞች! ወቅታዊ መረጃ ከማለዳ 12 ሰአት እስከ 3:30 በመላው ኢትዮጵያ 147 ሚሊዮን 965 ሺህ ችግኞች ተተክለዋል።
ሃምሌ 10 በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኞች! ወቅታዊ መረጃ ከማለዳ 12 ሰአት እስከ 3:30 በመላው ኢትዮጵያ 147 ሚሊዮን 965 ሺህ ችግኞች ተተክለዋል።
ኢትዮጵያውያን ዳግም ለትውልድ የሚሻገር ታሪክ ለምንሰራበት ቀን እንኳን አደረሰን! #GreenLegacy ኢትዮጵያዊያን ማቀድ፤ መተግበርና፤ በትጋት ሰርቶ መፈፀም ብቻ ሳይሆን የጀመርነውን ማስቀጠል እንደምንችል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በተግባር አሳይተናል ሲሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ ገለፁ፡፡ ሚኒስተር ዴኤታዋ ዛሬ በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል መርሃግብር መጀመርን አስመልክቶ አዲስ አበባ ከሚገኘው የሁኔታ መከታተያ ማዕከል መግለጫ…
የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በአስተማማኝ መሰረት ላይ ለመገንባትና በዋና ዋና ሃገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባትን ለመፍጠር የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ሥራዎች የተናበቡ ሊሆኑ እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ሚኒስትር ዲኤታ ተናገሩ፡፡ ሚኒስትር ዲኤታው አቶ ከበደ ደሲሳ ለሁለት ቀናት በአዳማ ሲካሄድ የነበረው የፌዴራል እና የክልል ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዓመታዊ የጋራ መድረክ ማጠቃለያ ላይ እንደተናሩት የሚዲያ እና የኮሙኒኬሽን ሥራዎች ከመቼውም ጊዜ በላይ በቅንጅት፣ በመናነብና…
ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ ዛሬ በአዳማ የፌዴራል እና የክልል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዓመታዊ የጋራ መድረክን ሲከፍቱ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በአሁኑ ወቅት ከአፍሪካ 5ኛ ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ደረጃ ላይ መገኘቱን ጠቅሰዋል፡፡ በሃገሪቱ የተመዘገቡት ዘርፈ ብዙ ስኬቶች ሁሉም ጠንካራ የሚዲያና እና የኮሙኒኬሽን ተግባቦት ሥራ ድጋፍ እንደነበራቸው የተናገሩት ሚኒስትሩ ስኬቶቹ ግን በርካታ ፈተናዎችም እንደነበሩባቸው ጠቁመዋል፡፡ በተለይም ጽንፈኝነትና አክራሪነት እንደ…
በተለያዩ ክልሎች አርሶ አደሩ የሚያነሳውን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ጥያቄ ምላሸ ለመስጠት መንግስት በ2015 ዓ.ም ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን በላይ የአፈር ማዳበሪያ ግዢ ፈጽሟል፡፡ መንግስት ለዓመቱ ገዥ እንዲፈጸም ካደረገው የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ ከ669 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ አገር ውስጥ ተጓጉዞ ካለፈው ዓመት ከተረፈው 210 ሺህ ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ ጋር ተጨምሮ ከ879…
በቅርቡ የአለም ምግብ ፕሮግራምና የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት USAID ለኢትዮጵያ የሚያቀርቡትን ሰብአዊ ድጋፍ ለጊዜው መግታታቸውን ማሳወቃቸው ይታወሳል። ከዚሁ ጋር በተገናኘ መንግስት ከአጋር አካላቱ ጋር በጋራ በመሆን የአሰራር ክፍተት አለባቸው የተባሉትን ለመፈተሽ፤ ማሻሻያ ለማድረግና ህገወጥ ተግባራትም ተፈፅመው ከተገኙ አጣርቶ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆኑን አሳውቋል። ይህንንም ተከትሎ በአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን መሪነት ከጉዳዩ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት…
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የክልል የኮሙኒኬሽን ተቋማት ያሉበትን ደረጃ ለማወቅና አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ በዘጠኝ ክልሎች እና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች ሲያካሂድ የቆየውን የክትትልና ድጋፍ ሥራ አጠናቋል፡፡ አገልግሎቱ ከተሰጡት ኃላፊነቶች መካከል የተቀናጀ እና የተናበበ የተግባቦት ሥራ ከፌዴራል እና ከክልል ኮሙኒኬሽን ተቋማት ጋር መዘርጋት፣ በትብብር መሥራት እና ለክልል የኮሙኒኬሽን ቢሮዎች የተግባቦት ሥራን ለማከናወን የሚያስችል አቅም መገንባት ይገኝበታል፡፡ ይህንን ኃላፊነቱን…
መንግስት ሂዩማን ራይትስ ዎች ያወጣውን ሪፖርት አስመልክቶ ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ምላሹም እንደሚከተለው ይቀርባል፡- ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው ድርጅት እ.ኤ.አ. ጁን 1 ቀን 2023 (ግንቦት 24 ቀን 2015 ዓ.ም) በሀገራችን በአንዳንድ አካባቢዎች ጉልህ የሆኑ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መፈጸማቸውን የሚገልጽ መሰረተ ቢስ ሪፖርት አውጥቷል ብሏል። በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ግጭት በርካታ አካባቢዎችን ለጉዳት ያጋለጠ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ የተወሰነ…
በሐረር ከተማ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ተገንብቶ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘውን የሐረሪ ክልል ባህል ማዕከልን የጋዜጠኞችና የኮሙኒኬሸን ባለሙያዎች ቡድን ዛሬ ጎብኝቷል፡፡ የባህል ማዕከሉ የወጣቶችን ስብዕና ለመገንባት እንዲሁም ስለ ሃገራቸውና ስለ ሃረሪ ክልል ባህላዊና ታሪካዊ እሴቶች ለማስተዋወቅ ያስችላል ተብሏል። ሐረር የመቻቻልና የፍቅር ከተማ መሆንዋን በተጨባጭ ለማሳየትና የቱሪዝም ማዕከልነቷን ለማሳደግ የባህል ማዕከሉ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የሐረሪ…
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና በህዝቡ ትብብር እየተገነቡ ያሉ የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ተቋማት የሕብረተሰቡን ተሳትፎ በእጅጉ ሊያሳድጉ የሚችሉ መሆናቸው ተገለጸ፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን ያዘጋጁት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ቡድን ጉብኝት በሁለተኛ ቀን ቆይታው በድሬዳዋ እየተከናወኑ ያሉ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውሮ ተመልክቷል። በዛሬው እለት የድሬዳዋ የወጣቶች ስፖርት አካዳሚ፣ የድሬዳዋ ስታዲየም ማሻሻያ ፕሮጀክት፣ የድሬዳዋ…