በኦሎምፒክ መድረክ ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ የ15 አትሌቶቻችን የክብር ሐውልቶችን የያዘው ‘አዲስ ስፖርት ፓርክ’!
https://www.facebook.com/share/v/14beQYsbHVv
ምክንያቱም ህፃናት በትምህርታቸውና በህይወታቸው ስኬታማ እንዲሆኑ የሚያስፈልጋቸውን ክህሎትና እውቀት በማስጨበጥ ለዘላቂ ትምህርትና ለግል ስኬታማነት መሰረት ይጥላል። ጥራት ያለው የቅድመ-መደበኛ ትምህርት ተደራሽነትን ለማስፋፋት፣ መምህራንን ለማሰልጠን፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ምቹ የመማሪያ አካባቢን ለመፍጠር በሀገር አቀፍ ደረጃ በሺዎች የሚቆጠሩ የመዋለ ህፃናት ትምህርት ቤቶች እየተቋቋሙ ይገኛሉ። ቅድመ መደበኛ ትምህርት አገልግሎት ባልተዳረሰባቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ዘንድ በመድረስ እኩልነትን ያረጋግጣል፣ ማህበራዊና የአስተሳሰብ እድገትን…
መገናኛ ብዙሃን በግብርናው ዘርፍ የተገኙ ውጤቶችንና አዳዲስ የምርምር ስራዎችን በተገቢው መልኩ ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ሊያደርጉ እንደሚገባ ተገለጸ። መንግስት የሃገሪቱን ሰላምና ደህንነት ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ትልቁ ትኩረቱ ምርታማነትን ማሳደግ በመሆኑ ሕብረተሰቡ ሙሉ ትኩረቱን ወደ ልማት እንዲመልስ ለማድረግ የመገናኛ ብዙሃን የበኩላቸውን ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ ተናገሩ፡፡ ዛሬ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ከፍተኛ አመራሮችና…
መላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለጳጉሜ 5 የነገ ቀን እና ለአዲሱ ዓመት ዋዜማ በሠላም አደረሳችሁ! ነገ የጊዜ መቍጠሪያ ብቻ አይደለም፤ ነገ ተስፋ፣ ምኞት፣ ስንቅ፣ ለዛሬ መነሣሣትና ትጋት ምክንያት ጭምር ነው፡፡ ነገ ሁላችንም ለማየት የምንጓጓለት፣ የተሻለ ሕይወትና ስኬት እንዲኖረን የምንመኘዉ መሻታችን ነው፡፡ እንደግለሰብ የተሻለ ነገን እንመኛለን፤ እንደቤተሰብ የተሻለና የጋራ ደስታና ተድላ ያለው ነገን እናልማለን፤ እንደሀገር ሰላም፣ ደስታ፣ ብልጽግና…
ኢትዮጵያ በአህጉራዊ የፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ እና በዲፕሎማሲያዊ ሚናዋ አፍሪካ የአንድነት ድምፅ እንዲኖራት እያደረገች ያለችው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የአገልግሎቱ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ በመግለጫቸው እንዳመለከቱት፣ ሀገራችን በሰላም ማስከበር ስምሪቶች ቀዳሚ ተሳትፎ በማድረግ፣ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) ስምምነትን በፍጥነት በማጽደቅ እና ለተለያዩ አህጉራዊ ተቋማት የመሠረተ ልማት ድጋፍ በማቅረብ ረገድ ያላትን…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአምራች ኢንዱስትሪው የታለመለትን ብሔራዊ ግብ እንዲመታ አስተማማኝ የሎጂስቲክስ መዋቅርና የባህር በር አማራጮች መኖራቸው አማራጭ የሌለው ወሳኝ ጉዳይ ነው። ምርቶችን በብዛትና በጥራት ማምረት በራሱ በቂ አይደለም ዋናው ቁምነገር ያመረቱትን ውጤት በብቃት፣ በቅልጥፍና እና በተወዳዳሪነት ለዓለም አቀፍ ገበያ ማድረስ መቻል ነው።ከዚህ አንጻር የኢትዮጵያ የራሷ የሆነ ወይም በውል የተረጋገጠ የባህር በር የማግኘት ጥያቄ…
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የክልል የኮሙኒኬሽን ተቋማት ያሉበትን ደረጃ ለማወቅና አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ በዘጠኝ ክልሎች እና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች ሲያካሂድ የቆየውን የክትትልና ድጋፍ ሥራ አጠናቋል፡፡ አገልግሎቱ ከተሰጡት ኃላፊነቶች መካከል የተቀናጀ እና የተናበበ የተግባቦት ሥራ ከፌዴራል እና ከክልል ኮሙኒኬሽን ተቋማት ጋር መዘርጋት፣ በትብብር መሥራት እና ለክልል የኮሙኒኬሽን ቢሮዎች የተግባቦት ሥራን ለማከናወን የሚያስችል አቅም መገንባት ይገኝበታል፡፡ ይህንን ኃላፊነቱን…