#ኢትዮጵያ_በዚህ_ሳምንት
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
“የዩናይትድ ኪንግደም የኮመንዌልዝ፣ ልማት ጉዳዮች እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተከበሩ ይቬት ኩፐርን አግኝቼ በቁልፍ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተናል። ከውይይታችን ጎን ለጎን በተካሄደው የኢንቨስትመንት አማካሪዎች ማህቀፍ ሥር የኢንቨስትመንት እና ኃብት አስተዳደር የቴክኒካል ትብብር የመግባቢያ ሥምምነት እና የሁለት የጋራ የልማት ስምምነቶች ፊርማ መርሃ ግብር ላይም ተገኝተናል። እነዚህም የሁርሶ-አይሻ 400 ኪሎ ቮልት እና የደገሃቡር-ቀብሪደሃር 132 ኪሎ…
በኢትዮጵያ በመከናወን ላይ ያሉ የመኖሪያ ቤት ልማት ሥራዎች በቤተሰብ ደረጃ ደህንነታቸው የተጠበቀ፣ ዘላቂ እና አስተማማኝ መኖሪያዎችን በማስፋት የኑሮ ሁኔታን በማሻሻል ላይ ይገኛሉ ምንም እንኳን የመኖሪያ ቤት ፍላጎት አሁንም ከፍተኛ ቢሆንም፥ የኢትዮጵያ መንግሥት መደበኛ የቤት አቅርቦትን ከማህበራዊ ድጋፍ ጋር በማቀናጀት ሰፊ ስራዎችን እየከወነ ይገኛል። ቀጣይነት ካላቸው የከተማ እና የህብረተሰብ ተኮር የቤት ልማት መርሃ ግብሮች በተጨማሪ፤ ዓመታዊው…
“ከደቡብ አፍሪካ የቀድሞ ፕሬዝደንት ታቦ ምቤኪ ጋር በአፍሪካ ልማት፣ በቀጠናዊ ትስስር እና አኅጉራዊ የቅድሚያ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገናል።” ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication Post Views: 50
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2027 የሚካሄደውን 32ኛውን የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ COP32 እንድታስተናግድ መመረጧ፤ የሀገሪቱን ዓለም አቀፋዊ ተሰሚነት ለማሳደግ፣ በመሰረተ ልማት እና በአረንጓዴ ልማት ዘርፎች ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል። ዓለም አቀፍ መሪዎች፣ ባለሀብቶች እና ድርጅቶች የሚታደሙበት ይህ ታላቅ ሁነት፤ የኢኮኖሚ እድገትን ያነቃቃል፣ የሥራ ዕድል ይፈጥራል እንዲሁም የሀገር ውስጥ ንግድን ይደግፋል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በሕዝብ አገልግሎቶች እና…
የካቲት 20/2018 ዓ.ም የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አመራሮችና ሠራተኞች 130ኛውን የዓድዋ ድል በዓል “ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል መሪ ቃል በድምቀት አክብሯል። በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ እንደገለጹት፣ ከ130 ዓመታት በፊት አባቶቻችን ለትውልድ የሚተርፍ አኩሪ ታሪክ ሰርተው እንዳስቀሩ ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን በወቅቱ ድል ሊቀዳጁ የቻሉበትን ዋና ምክንያት…
በኢትዮጵያ የጂኦ-ቱሪዝም እምቅ ሀብቶቿን በዩኔስኮ ዓለም አቀፍ የጂኦ-ፓርክነት በማስመዝገብ ተጠቃሚነቷን ለማሳደግ የዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል ። ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላት ያልተነካ ሀብት በጂኦ-ቱሪዝም ተመራጭ ሀገር የሚያድርጋት ነው። ከዚህ አንጻር ለዩኔስኮ በወደፊቱ ሊቀርቡ የሚችሉ በርካታ የሀገሪቱ እጩ የጂኦ-ቅርስ ቦታዎች ተለይተዋል። ከነዚህም ውስጥ በባሌ ወረዳ የሚገኘው ሶፍ-ዑመር ዋሻ፣ በቡታጅራ-ስልጤ የሚገኙት አፈጣጠሮች፣ የሰሜንና የገራልታ ተራሮች፣ የደናክል ስምጥ ሸለቆ፣ ኤርታ…
