የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
“አብዛኛው አሁን ያለንበት ችግር፤ የማይሰሩ እጆች፣ በሚናገሩ አፎች ብቻ ተይዘው ልማት የሚመጣ፣ ሰላም የሚመጣ፣ ብልጽግና የሚረጋገጥ ይመስላቸዋል።”
“አብዛኛው አሁን ያለንበት ችግር፤ የማይሰሩ እጆች፣ በሚናገሩ አፎች ብቻ ተይዘው ልማት የሚመጣ፣ ሰላም የሚመጣ፣ ብልጽግና የሚረጋገጥ ይመስላቸዋል።”
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 5/2017(ኢዜአ)፦ መገናኛ ብዙሃን ኢትዮጵያ የምታስተናግደውን የተመድ የሥርዓተ ምግብ ጉባኤ ሀገራዊ ፋይዳ በመገንዘብ የተደራጀ መረጃ ተደራሽ ሊያደርጉ እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ገለጹ። ኢትዮጵያ 2ኛውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሥርዓተ-ምግብ ጉባኤን ከሁለት ሳምንት በኋላ ታስተናግዳለች። የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት መገናኛ ብዙሃን ጉባኤውን በተመለከተ ሊኖራቸው የሚገባው ግንዛቤ እና የሥርዓተ ምግብ ሽግግር ፅንሰ…
ቢኒያም ኤሮ ፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ በኢትዮጵያ የዘመናዊ ሚዲያ ታሪክ ፈር ቀዳጁና የጥንቱ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ የነበሩበትን ዘርፈ ብዙ ተግዳሮቶች ለመፍታት የለውጡ መንግሥት በዘርፉ ያደረገው ሪፎርም ተቋሙ ዓበይት የለውጥ እመርታዎችን እንዲያሳይ በር ከፋች ነበር ሲሉ አካፍለዋል። መዋቅራዊ ክፍተቶች፣ ግልጽ ያልሆነ ኤዲቶርያል ፖሊሲ፣ የብዝሃነትና ተደራሽነት ፈተና እንዲሁም የቴክኖሎጂ ኋላ ቀርነት ተቋሙን የፈተኑት ማነቆዎች…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአምራች ኢንዱስትሪው የታለመለትን ብሔራዊ ግብ እንዲመታ አስተማማኝ የሎጂስቲክስ መዋቅርና የባህር በር አማራጮች መኖራቸው አማራጭ የሌለው ወሳኝ ጉዳይ ነው። ምርቶችን በብዛትና በጥራት ማምረት በራሱ በቂ አይደለም ዋናው ቁምነገር ያመረቱትን ውጤት በብቃት፣ በቅልጥፍና እና በተወዳዳሪነት ለዓለም አቀፍ ገበያ ማድረስ መቻል ነው።ከዚህ አንጻር የኢትዮጵያ የራሷ የሆነ ወይም በውል የተረጋገጠ የባህር በር የማግኘት ጥያቄ…
*************************** የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት እና የሩሲያው አርቲ በጋራ በሚሠሩባቸዉ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ምክክር አድርገዋል፡፡ የአርቲ ዋና ዳይሬክተር እና ሌሎች ከፍተኛ ኃላፊዎችን በጽሕፈት ቤታቸዉ ተቀብለው ያነገጋሩት የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወ/ሮ እናትዓለም መለሰ የኢትዮጵያ መንግሥት የአፍሪካን ድምፅ አጉልተዉ ከሚያሰሙ እና ሚዛናዊና ትክክለኛ የአህጉሪቱን ትርክት ከሚያንፀባርቁ የሚዲያ ተቋማት ጋር በቅርበት እንደሚሠራ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ እንደ ሀገር…
ከወራት በኋላ በአዲስ አበባ በሚካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያን በጎ ገፅታ ለመገንባት የተቀናጀ የኮሚኒኬሽን ሥራ እንደሚያስፈልግ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ገልፀዋል። ሚኒስትር ዴኤታው ይህንን የገለፁት በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለሚሳተፉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነባር ዲፕሎማቶችና በጎ ፍቃደኛ ካዴቶች በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ተገኝተው በውጤታማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን…
ባለፉት ሀምሳ ዓመታት የኢትዮጵያ ሴቶች ከፍፁም መገለል ተነስተዉ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊና በልማት መስኮች የባለቤትነት ዋስትናን አረጋግጠዋል፡፡ ዛሬ ላይ ሴቶች በሀገሪቱ የፖለቲካ ዐዉድና ልማት ዘርፎች ውስጥ ግንባር ቀደም ሚናን እየተጫወቱም ይገኛሉ፡፡ ይህ ለውጥ የሴቶችን መሠረታዊ መብቶች ከማስጠበቅ ባለፈ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ገጽታ ላይ የሚታዩ ውጤቶችን እንዲጎናጸፉ አስችሏቸዋል፡፡ ሴት መሪዎች ፖሊሲዎችን በመቀረጽ፣ የአገልግሎት አሰጣጥን በማሳለጥ፣ ልማትን በማፋጠን፣ እንዲሁም…
