በተባበረ ክንድ የኢትዮጵን ብልፅግና እዉን እናደርጋለን፡፡ ‘

ዓለም አቀፍ “የመታወቅ ቀን” በመስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ይገኛል፡፡ መታወቂያ ማግኘት የዜጎች መብት ብቻ ሳይሆን ሰብዓዊ መብት እንደመሆኑ መሠረታዊ አገልግሎትን ለማግኘት ፥ መብትን ለማስጠበቅ እና በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች ሙሉ ተሳትፎ ለማድረግ አስፈላጊ ስለሆነ፣ሁሉም ሰው መታወቅ ይገባዋል፣ሁሉም ሰው የመታወቅ መብት አለው። እ.ኤ.አ ሴፕቴምበር 16 ቀን የሚከበረው ዓለም አቀፍ “የመታወቅ ቀን” ዘንድሮ…
ከወራት በኋላ በአዲስ አበባ በሚካሄደው 38ኛው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያን በጎ ገፅታ ለመገንባት የተቀናጀ የኮሚኒኬሽን ሥራ እንደሚያስፈልግ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ገልፀዋል። ሚኒስትር ዴኤታው ይህንን የገለፁት በ38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለሚሳተፉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነባር ዲፕሎማቶችና በጎ ፍቃደኛ ካዴቶች በአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ተገኝተው በውጤታማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን…
ሃምሌ 10 በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኞች! ወቅታዊ መረጃ ከማለዳ 12 ሰአት እስከ 3:30 በመላው ኢትዮጵያ 147 ሚሊዮን 965 ሺህ ችግኞች ተተክለዋል። Post Views: 926
“ኢትዮጵያ ለሁለንተናዊ ጉዳዮች ጥንቃቄ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ትገኛለች። በሚዲያ ሥራ ጥረቶቻችን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም፣ ሰላም እና ፍቅር ቅድሚያ ሰጥተን መሥራት ይገባናል። ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር ምን ጠቃሚ ሥራ እየሠራን ነው ብለን ራሳችንን ሳናሰልስ መጠየቅ አለብን። በዛሬው ዕለት ሀገራዊ ልማት እና ኅብረትን በማስተዋወቅ ብሎም ብሔራዊ ጥቅምን በማስጠበቅ ጥረት ረገድ ከፍ ያለ ሥራ በመሥራት ሽልማት ለተበረከተላቸው የሚዲያ ተቋማት…
በርካታ ሃገራዊና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎች ቢያጋጥሙም በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በባለፉት ስድስት ወራት ውጤታማ ሥራዎችን ለመስራት መቻሉንም አንስተዋል። ይህንን ለማሳካት ለደከሙ የዘርፉ ተዋንያን በሙሉም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የፌዴራልና የክልል የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት የግማሽ አመት የጋራ ጉባኤ ዛሬ በአዳማ ከተማ ተጀምሯል። በኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት በሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በልማት፣ በመልካም አስተዳደርና በሰላም አጀንዳዎች ዙሪያ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የተሰራው…
መንግስት ሂዩማን ራይትስ ዎች ያወጣውን ሪፖርት አስመልክቶ ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ምላሹም እንደሚከተለው ይቀርባል፡- ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው ድርጅት እ.ኤ.አ. ጁን 1 ቀን 2023 (ግንቦት 24 ቀን 2015 ዓ.ም) በሀገራችን በአንዳንድ አካባቢዎች ጉልህ የሆኑ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መፈጸማቸውን የሚገልጽ መሰረተ ቢስ ሪፖርት አውጥቷል ብሏል። በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ግጭት በርካታ አካባቢዎችን ለጉዳት ያጋለጠ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ የተወሰነ…