የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ተኛ የስራ ዘመን የጋራ ጉባኤ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴን የኢፌዴሪ መንግስት ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል።

አዲሱ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ የኢፌዴሪ ህገ መንግስትን ከቀድሞዋ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተረክበዋል።


አዲሱ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ የኢፌዴሪ ህገ መንግስትን ከቀድሞዋ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተረክበዋል።
በግብርና ዘርፍ ያገኘናቸው ስኬቶች በኢንዱስትሪው ዘርፍም በመደገም ላይ ናቸው። የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የሀገር በቀል አነስተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም አሳድጓል ንቅናቄው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ለመተካት፣ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በጥራትና በብዛት ለማምረት እንዲሁም የግብርና እና ማዕድን ምርቶች ላይ ዕሴት ጨምሮ ለገበያ ለማቅረብ አዲስ ምዕራፍም ከፍቷል።በተለይ በጎጆ ኢንዱስትሪ የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት እንቅስቃሴ አካል የሆነው የገቢ ምርቶችን…
ኅብረ ብዙ ኢትዮጵያውያንና ትውልድ ኢትዮጵያውያን እንኳን ለኅብር ቀን በሰላም አደረሳችሁ! ጳጕሜን 4 የኅብር ቀን “ኅብራችን ለሰላማችን” በሚል መሪ መልዕክት ተከብሮ ይውላል፡፡ በእርግጥም የኅብር ቀን ኢትዮጵያውያን ዓመቱን ሙሉ ልናከብረዉ የሚገባ ነው፤ ኅብራችን ብዙ ነውና፡፡ በብሔር፣ በቋንቋ፣ በአመለካከት፣ በመልክዓ ምድር፣ በአመጋገብ፣ በአኗኗር ዘይቤ፣ በአለባበስ ወ.ዘ.ተ፡፡ ኅብራዊነታችን ሰፊ ነው፡፡ ይህ ኅብራችን ደግሞ ውበታችን፣ ሀብታችን፣ የደስታና የጥንካሬያችን ምንጭ ነው፡፡…
የኮሙኒኬሽን ሥራዎቻችን የበላይነትን ይዘው እንዲቆዩ የመንግስትን ዋና ዋና አጀንዳዎች በሚገባ መለየትና በእቅድ አካቶ መስራት እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ ተናገሩ፡፡ ሚኒስትሩ በአዳማ እየተካሄደ በሚገኘው “ውጤታማ ተግባቦት ለኢትዮጵያ ልዕልና” የስልጠና መርሃ ግብር ላይ “የሕዝብ ግንኙነትና መሰረቶች፣ አጀንዳ ቀረጻና የቀውስ ጊዜ ኮሙኒኬሽን” በሚል ርዕስ የስልጠና ሰነድ አቅርበው ውይይት ተደረጎበታል። ከሃገራዊ አበይት እቅዶች ጋር በማጣጣም…
መንግስት ሂዩማን ራይትስ ዎች ያወጣውን ሪፖርት አስመልክቶ ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ምላሹም እንደሚከተለው ይቀርባል፡- ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው ድርጅት እ.ኤ.አ. ጁን 1 ቀን 2023 (ግንቦት 24 ቀን 2015 ዓ.ም) በሀገራችን በአንዳንድ አካባቢዎች ጉልህ የሆኑ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መፈጸማቸውን የሚገልጽ መሰረተ ቢስ ሪፖርት አውጥቷል ብሏል። በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ግጭት በርካታ አካባቢዎችን ለጉዳት ያጋለጠ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ የተወሰነ…
የዛሬ ጀምበር ወጥታ እስክትጠልቅ ስድስት መቶ ሚሊዮን ችግኞችን ልንተክል ኢትዮጵያውያን ሁሉ አቅደን ነበር። ያሰብነውን ሳናሳካ ጀምበር የሚጠልቅብን አይደለንምና በአንድ ጀምበር 615.7 ሚሊዮን ችግኞችን መትከል ችለናል። ህፃናት ተስፋቸውን ተክለዋል። ወጣቶች ጽናተቸውን አሳይተዋል። አረጋውያን ውርስ አኑረዋል። ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ ከቤታቸው ወጥተው የማይደበዝዝ አሻራ አኑረዋል። በማበራችን እና በመጽናታችን በአለም በሌላ ስፍራ በአንድ ጀምበር ያልተደረገውን እኛ ኢትዮጵያውያን አድርገነዋል።…