የህዳሴ ግድብ በተርባይን ከሚያልፈው ውሃ በተጨማሪ በግድቡ ውሃ ማስተንፈሻ በሮች / Spillway/ በአንድ ሰከንድ 2800 ሜትር ኪዮብ ውሃ ወደ ተፋሰስ ሀገራት መልቀቅ ጀምራል።

ዓለማችን ዛሬ ትላንት የምናውቃት አይደለችም፡፡ ነገሮች በፍጥነት እየተለዋወጡ ቴክኖሎጂው እየፈጠነ ዓለም ውድድርና እሽቅድድም ውስጥ ገብታለች፡፡ ይህም ሆኖ አንዱ አንዱን ቀድሞ ለማለፍ በሚደረጉ ጥሩጫዎች ውስጥ ቴክኖሎጂውን ለመልካም የመጠቀሙ እድል እንዳለ ሆኖ ቴክኖሎጂ ለጥፋትም እየዋለ እንመለከታለን፡፡ በአሁኑ ወቅት በዓላማችን ላይ በርካታ የመሣሪያ ጦርነቶች እየተካሄዱ ነው፡፡ የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት እልባት ሳያገኝ የእስራኤልና የሀማስ ጦርነት ዓለምን እየፈተናት ይገኛል፡፡ በአፍሪካ…
የሰላምን አማራጭ የተከተሉ የትኞቹም ቡድኖች በሀገረ መንግሥት ግንባታ ጥረት በንቃት እንዲሳተፉና የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ መንግሥት አስፈላጊውን ሁሉ ለማድረግ ጽኑ ፍላጎት አለው ሲሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ። ለሰላም አዎንታዊ ምላሽ የሰጡ የቀድሞ ታጣቂዎች ሀገሪቱ በያዘችው የሰላምና የብልጽግና ጉዞ ሂደት ውስጥ ሊጫወቱ የሚችሉትን ወሳኝ ሚና መንግሥት ይገነዘባል ብለዋል ሚኒስትሩ ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)። የሰላም አማራጭን…
ሰላማዊት ካሳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ ሚኒስትር ዴኤታዋ ሰላማዊት ካሳ መንግስት ማህበረሰቡ የሚያነሳቸውን የተለያዩ ጥያቄዎች ለመስማት ከሚያደርገው ጥረት አንዱ ከመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች ጋር የመስክ ምልከታ ማድረግ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በሀዋሳ የመስክ ምልከታ እያረጉ ሲሆን በዚህ የመስክ ምልክታ ከተሞች የነዋሪዎችን ፍላጎትና የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች መመለስ እንዲችሉና የቱሪስት ቁጥርን ማስተናገድ በሚያስችል መልኩ…
መላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለጳጉሜ 5 የነገ ቀን እና ለአዲሱ ዓመት ዋዜማ በሠላም አደረሳችሁ! ነገ የጊዜ መቍጠሪያ ብቻ አይደለም፤ ነገ ተስፋ፣ ምኞት፣ ስንቅ፣ ለዛሬ መነሣሣትና ትጋት ምክንያት ጭምር ነው፡፡ ነገ ሁላችንም ለማየት የምንጓጓለት፣ የተሻለ ሕይወትና ስኬት እንዲኖረን የምንመኘዉ መሻታችን ነው፡፡ እንደግለሰብ የተሻለ ነገን እንመኛለን፤ እንደቤተሰብ የተሻለና የጋራ ደስታና ተድላ ያለው ነገን እናልማለን፤ እንደሀገር ሰላም፣ ደስታ፣ ብልጽግና…
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና በህዝቡ ትብብር እየተገነቡ ያሉ የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ተቋማት የሕብረተሰቡን ተሳትፎ በእጅጉ ሊያሳድጉ የሚችሉ መሆናቸው ተገለጸ፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን ያዘጋጁት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ቡድን ጉብኝት በሁለተኛ ቀን ቆይታው በድሬዳዋ እየተከናወኑ ያሉ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውሮ ተመልክቷል። በዛሬው እለት የድሬዳዋ የወጣቶች ስፖርት አካዳሚ፣ የድሬዳዋ ስታዲየም ማሻሻያ ፕሮጀክት፣ የድሬዳዋ…
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ ከሰሞኑ ባጋጠመው የመሬት መንሸራተት አደጋ በሰው ህይወትና ንብረት ላይ በደረው ጉዳት የኢፌዴሪ መንግሥት የተሰማዉን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻል፡፡ ለተጎጂ ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶችም መፅናናትን ይመኛል፡፡ ባጋጠመው አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውን ተጎጂዎች ለመታደግ፣ በናዳ ውስጥ የተቀበሩ ሰዎችን ለማፈላለግ፣ የነብስ አድን ሥራዎችን ለማከናወን እንዲሁም ጉዳት የደረሰባቸዉን ዜጎች መልሶ…