ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እድሳት የተደረገለትን የፋሲል ግቢ በሚመርቁ ወቅት ያስተላለፉት መልዕክት:-

👉የጎንደር ህዝብ ታላቅ በሆነው በዚህ ደስታው ተካፋይ እንድንሆን ስለፈቀደልን እናመሰግናለን ።

👉ጎንደር ሽማግሌዎች አሏት ባዕድ ሳይሆን ባላገሮች፣ ባለቤቶች እንኳን ከአንድ ሰፈር ወደ ሌላ ሰፈር ተንቀሳቅሰው የሀገራቸውን ልማት ማየት፣ ማገዝ እንዲችሉ ሰላም ያስፈልጋል ።

👉የወጡ ወንድሞቻችን ጊዜ ማባከን የለባቸውም፤ የሚያስፈልገን ተመልሰው በአንድነት እና በትብብር መሥራት፣ ሀገር ማልማት አለብን ።

👉ዛሬ ጎንደርን፣ ባሕርዳርን ወይም አማራ ክልልን ከአማራ ተወላጆች በስተቀር ማንም አያዝበትም ።

👉እኛ የክልሉን ልማት ከማገዝ በቀር በዕለት ተዕለት ጉዳይ እና ሥራዎች ውስጥ እጃችንን አናስገባም ። ይህ ዕድል ኢትዮጵያ ውስጥ አልነበረም ፤ አሁንም ይህን ዕድል ከምናበላሸው በትብብር መንፈስ ብንሠራ የገራአችን፣ የልጆቻችን ነገ ያማረ ይሆናል ።

👉ጎንደር፣ ባሕርዳር፣ አማራ፣ ኢትዮጵያ ዳግም እንዲወለዱ በትብብር መንፈስ በጋራ እንድንቆም አደራ ልላችሁ እፈልጋለሁ

👉የፋሲል ቤተመንግሥት ዕድሳትን በተመለከተ

ይህን የመሰለ ስጦታ የሰጡን አባቶቻችን የነሱን ፈለግ ተከትለን ሀገር ብናለማ ሀገር ብንሰራ ዛሬ ኢትዮጵያ ተረጂ አትሆንም ነበር ።

👉 የታላቆችን ስራ ማድነቅ፣ ማክበር እና መመርመር መጀመር ለዛ ስራ አንድ ጡብ ወደ ማስቀመጥ ያሸጋግራል ።

👉ትናንትናችን ማስታወሻችን መታወሻችን በመሆኑ ሰው ማስታወሻውን መታወሻውን አይዘነጋም። ኋላውን ማስታወስ የቻለ ሰው እና ማህበረሰብ ዛሬን ለመነሻነት እና ለመስሪያነት ይገለገላል ።

👉በጎንደር ከተማ የተጀመሩ ስራዎች እና በፋሲል ቤተ መንግስት ግቢ ውስጥ የታየው ለውጥ ልጆቻን ከኛ የተሻለ ተስፋ እንዳላቸው ማሰብ ብቻ ሳይሆን በሚጨበጥ ነገር ለማየት ያስችላል።

👉የጎንደር ልጆች አባቶች ያስረከቡትን እና ዛሬ የተሰራውን ስራ የበለጠ በሚያልቅ መልኩ በመስራት የበለጠ ያማረ፣ የተዋበ እና የለማ ሀገር ለመፍጠር ሥሩ ።

👉ፋሲል ቤተ መንግስት መጠገን እና መታደስ ብቻ ዳግም ነው የተወለደው ።

👉እንደ ፋሲል ዳግም ውልደት ሁሉ ጎንደር ዳግም እንድትወለድ የሁላችንም መሻት እና ስራ ሊሆን ይገባል ።

👉ጎንደር ዳግም ተወልዳ ለዓለም አሸብራቂ ከተማ እስክትሆን ድረስ ሁላችንመ በጋራና በትጋት እንሥራ ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Similar Posts