ከቀውስ ባሻገር መሻገር !!!

ሚያዝያ 21/2018 ዓ.ም በመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነትና በሆርሙዝ ወሽመጥ መዘጋት ምክንያት ዓለም አቀፉ የነዳጅ አቅርቦት ተቋርጦ፣ የበርካታ ሀገራት ማደያዎች እየተዘጉና ማኅበራዊ ቀውሶች እየተባባሱ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ በተወሰነም ደረጃ ቢሆን ይህንን ከባድ ፈተና መቋቋም የቻለችው መንግሥት ላለፉት ስምንት ዓመታት በታዳሽ ኃይል (ውኃ፣ ነፋስ፣ ፀሐይና ጂኦተርማል) ላይ ባከናወናቸው ግዙፍ ስትራቴጂያዊ ፕሮጀክቶች ነው። የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የተለያዩ የኃይል አማራጮችና የኤሌክትሪክ…

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

‎”የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ’’ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውና በማህበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የቀረቡበት የምክክር መድረክ ተገኝቼ ሃሳቤን አጋርቻለው። ‎‎የማህበራዊ ዘርፍ ግንባታ እንደ ሌሎች መሠረተ-ልማቶች ውጤቱ ወዲያው የሚታይና የሚጨበጥ ባይሆንም፣ ለሀገር ዘላቂና ወሳኝ መሰረት የሚጥል ነው። ኢትዮጵያ በሚገጥሟት ተግዳሮቶች ሳትገደብ ከሚገመተው በላይ በከፍተኛ ፍጥነት እየተገነባች ሲሆን፣ ምንም እንኳ የዐቅም ውስንነቶች ቢኖሩብንም ለማሻሻል…

‎የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ’’ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውና በማህበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የቀረቡበት የምክክር መድረክ፤ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።

‎በዚህም ባለፉት ዓመታት በማህበራዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ወሳኝ ስኬቶች ቀርበዋል። ‎በስምንት የለውጥ ዓመታት፤ ኢትዮጵያ በመሰረታዊና ማህበራዊ ዘርፎች የተስተዋሉ ክፍተቶች ላይ ትኩረት በማድረግ፤ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ሰፊ ሥርዓታዊ ሽግግር አድርጋለች። ‎በትምህርት ዘርፍ አዲስ ሥርዓተ-ትምህርትን በመተግበር፣ የመማሪያ መጽሐፍት ስርጭትን በማሻሻል እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርትና የሀገር አቀፍ ፈተና ሥርዓቶችን በማዘመን፣ የትምህርት ዘርፉ ጥራትና ተዓማኒነት እንዲላበስ ተደርጓል። ‎በተመሳሳይ የጤናው ዘርፍ ለ30…

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በሚኒስትር መስሪያቤታቸው የተመዘገቡ ዐበይት ስኬቶችን አቅርበዋል።

‎በዚህም ዘርፉ ከለውጡ በፊት ሲቸገርበት የነበሩ መጠነ ሰፊ ክፍተቶችን በመለየት ፈጣን መፍትሔ በመስጠት ሰፊ ስኬቶችን አስመዝግቧል።‎‎ከተገኙ ስኬቶች መካከል ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፦‎የፖሊሲና የህግ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት የዜጎችን መብት ጥበቃ፣ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ። አደረጃጀቶችን በመደገፍና በማጠናከር መብትና ግዴታ በማወቅ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ፣ የአቅመ ደካማ ዜጎችን የመደገፍና የማገዝ ባህል ማሳደግ ጥቂቶቹ ናቸው።‎እነዚህ ስኬቶች ቁጥር ብቻ ሳይሆኑ በተጨባጭ 4,330,948 የሚሆኑ…

የሥራና ክህሎት ሚኒስትሯ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል፤ በስራና ክህሎት ዘርፍ በለውጡ ዓመታት ኢትዮጵያ ያስመዘገበችውን ስኬቶች አብራርተዋል።

ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት በማድረግና ብቁ የሰው ሀብት እንዲሁም ምቹ እና አስተማማኝ የሥራ ዕድል የተፈጠረባት ኢትዮጵያን ማየት የተለመው ይህ ዘርፍ፤ ከለውጡ በኋላ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የስራ ስመሪት እንዲሁም ዜጎች በቤት ውስጥ እና ባሉበት ሆነው በሚሰሯቸው ስራዎች አማካኝነት ለ19,872,846 ዜጎች የስራ እድል ፈጥሯል። ይህን ታላቅ ስኬት ለማስመዝገብ ያስቻለው፤ ኢንተርፕርነር ተቋማትን በመፍጠር፣…

የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በጤና ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶችን ባቀረቡት ሪፖርት፦

ዘርፉ ከለውጡ በፊት የነበሩ ክፍተቶችን በመለየት ካስመዘገባቸው ዋና ዋና ስኬቶች መካከል፤ ለ30 ዓመታት የቆየው የጤና ፓሊሲን በመከለስ፣ መከላከል ከሚለው መርህ በተጨማሪ አክሞ የማዳን ቁርጠኛ የፖሊሲ አመራር፣ የተቋም ግንባታ፣ የጤና መሠረተ ልማት ለውጦች፣ መድሃኒት፣ ክትባት እና የህክምና ግብዓቶች ምርት አቅርቦት እና ቁጥጥር ጭማሪ እንዲሁም የጤና ፋይናንስ እመርታ ቁልፍ እና ዋነኞቹ የለውጥ ስራዎች ናቸው። ‎በተለይም የወረርሽኝ ልየታ…

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በትምህርት ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶችን አቅርበዋል።

‎ከለውጡ በፊት የትምህርቱ ዘርፍ በእጅጉ የተጎዳ፣ ሰፊ እና አፋጣኝ ተሀድሶ ከሚያስፈልጋቸው ዘርፎች አንዱ ነበር። ዘርፉን በእጅጉ ተጭነውት ከነበሩ ችግሮች መካከል፤ የመሠረተ ልማት ጥራትና የግብዓት እጥረት፣ የተማሪ-መምህር፣ የተማሪ-ክፍል ጥመርታ አለመመጣጠን፣ ለትምህርት ዓይነቶች ብቁ የሆኑ መምህራን አለመኖር፣ የስርዓተ ትምህርት አግባብነትና የመጻህፍት ተደራሽነት ችግሮች፣ ኢ-ፍትሃዊነትና ኢ-እኩልነት፣ የትምህርት ሴክተሩ ትክክለኛነት መዳከም፣ ዝቅተኛ የቅድመ መደበኛ ትምህርት መኖር ከብዙ ማነቆዎች ጥቂቶች…

አሁን በመካሄድ ላይ!

‎ ‎‘’የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ’’ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው እና በማህበራዊ ዘርፍ ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡ ዐበይት ውጤቶች የሚቀርቡበት የምክክር መድረክ፤ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት መካሄድ ጀምሯል። ‎ባለፉት ስምንት አመታት በተለይም በትምህርት፣ ጤና፣ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በባህል፤ በኪነ-ጥበብና ስፖርት እንዲሁም በሴቶች እና ማሕበራዊ ጉዳዮች የተመዘገቡ ውጤቶች በስፋት የሚተነተኑበት መድረክ ነው። #PMOEthiopia…

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

“የበጋ መስኖ እርሻ፤ በምግብ ራሳችንን ለመቻል በሚደረገው ጉዞ ውስጥ የጸና መሰረትን የጣልንበት ምዕራፍ ነው። ‎የውሃ ሀብታችንን በአግባቡ በመጠቀም፣ ባልተቋረጠ ጥረት እና ቁርጠኝነት፣ የመልማት ጉዟችን አስተማማኝና ዘላቂ የሆነ የምግብ ዋስትና ወደምናረጋግጥበት ብሩህ ተስፋ እንደሚያሸጋግረን ጥርጥር የለውም።” ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ሽግግር ከምርት ሉዓላዊነት ወደ ቴክኖሎጂ ልዕልና !

ሚያዝያ 20/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ሽግግር በቁጥር ከሚገለጽ የኢኮኖሚ ዕድገት ፍላጎት በላይ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን በዘላቂነት የምናረጋግጥበት ወሳኝ ምሶሶ ነው ። መንግሥት የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ‘የሉዓላዊነት ልብ’ አድርጎ በመቅረጽ፣ መሠረታዊ ፍላጎቶቻችንን በራሳችን አቅም በመሸፈን ከውጭ ጫና እና ጥገኝነት ነፃ የሆነ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ ነፃነት ለመገንባት በከፍተኛ ቁርጠኝነት እየተጋ ይገኛል። ይህ መዋቅራዊ ሽግግር ተግዳሮቶችን ወደ ስትራቴጂካዊ ድል በመቀየር፣ የኢትዮጵያን…