ዲጂታል ኢኮኖሚን ወደ ምርታማነት የመቀየር ሂደት በኢትዮጵያ

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ የሆኑት ሚሪያም ሰዒድ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ተበታትነው የነበሩ አሠራሮችን በዲጂታል ማንነት፣ በክፍያ እና በዳታ ልውውጥ የተቀናጁ የኢኮኖሚ መዋቅሮች ውስጥ በማስገባት፣ የመንግሥት አገልግሎቶችን በማገናኘት እንዲሁም የሃገር በቀል አቅምን በጋራ በማሳደግ፣ ለሰው ሠራሽ አስተውሎት ምቹ የሆነ የኢኮኖሚ መሠረት እየጣለችና ይሄንኑ ሪፎርም ወደ ምርታማነት እየቀየረች እንደምትገኝ አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ አዲስ የከተማ ልማት ምዕራፍ ውስጥ እየገባች ትገኛለች

በገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ትዕግሥት ፍስሀ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ አዲስ የከተማ ልማት ምዕራፍ ውስጥ እየገባች ሲሆን፥ ትኩረቱም ከተሞችን ማሰፋፋት ላይ ብቻ ሳይሆን ምርታማነታቸውን ማሳደግ እንዲሁም ምቹ፣ ተወዳዳሪ፣ ሁሉን አቀፍና ዘመናዊ ከተሞች ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለጋራ ብልፅግና ቀጣይ ሞተር እንዲሆኑ ማድረግ ነው።

የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ የሀገር ውስጥ መረጋጋትንና ተዓማኒነትን መልሶ ማምጣቱ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር እዮብ ተካልኝ፤ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ የሀገር ውስጥ መረጋጋትንና ተዓማኒነትን መልሶ ማምጣቱን ገልጸው፤ ይህም የዋጋ ንረትን በመቆጣጠር፣ የውጭ ምንዛሪ ገበያውን ነፃ በማድረግ፣ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲን በማዘመን፣ እንዲሁም ለዘላቂና አካታች ዕድገት ጠንካራ መሠረት ለመጣል የፋይናንስ ዘርፉን በማጠናከር የተገኘ መሆኑን አብራርተዋል።

ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ከለውጥ ወደ ዘላቂ ሽግግር” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው የ “ኢትዮጵያ ታከናውናለች” ጉባኤ ላይ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል። በጉባኤው ላይ ባለፉት 8 ዓመታት የተከናወኑ ዋና ዋና የሪፎርም ስራዎች እና ያመጧቸው ተፅዕኖዎች ታይተዋል።

ከተመሠረተ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ፣ መሶብ የኢትዮጵያን የሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት መሠረታዊ በሆነ መንገድ ለውጦታል።

ውጤቶቹም በራሳቸው ይናገራሉ። #PMOEthiopia ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች

“ሁሉም የስራ ኃላፊዎች በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት፣ ድሮ ከምናደርገው በላይ ውጤታማ መሆናችንን ማረጋገጥ ያስፈልጋል።”

“ሁሉም የስራ ኃላፊዎች በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት፣ ድሮ ከምናደርገው በላይ ውጤታማ መሆናችንን ማረጋገጥ ያስፈልጋል።”

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች

የዲጂታል ለልህቀት’’ ጉባኤን ተከትሎ፣ በህብረት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ በመሳተፍ ዘላቂ ተስፋን ተክለናል! – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

“የኢትዮጵያ ሕዝብ ሲሰበሰብ፣ ጉልበቱን፣ ሀብቱን፣ ዕውቀቱን ሲደምር በጣም በርካታ ችግሮችን መፍታት ይችላል።”

“የኢትዮጵያ ሕዝብ ሲሰበሰብ፣ ጉልበቱን፣ ሀብቱን፣ ዕውቀቱን ሲደምር በጣም በርካታ ችግሮችን መፍታት ይችላል።”

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication