የፕሬስ መግለጫ

ኢትዮጵያዊነት ብያኔዉ የተሻለ ዓልሞ የላቀ ማሳካት ነው! ኢትዮጵያ የቀደምት ሥልጣኔ መነሻ፣ የጥቍር ሕዝቦች የነፃነት ቀንዲል ብቻ አይደለችም፤ ኢትዮጵያ የመጪዉ ትውልድ የተስፋ ምድር ጭምር ናት፡፡ ኢትዮጵያውያን ደግሞ በጋራ ሉዓላዊነትን ከማስከበር ባሻገር የሚገለጹ፣ የመቻል ተምሳሌቶች ናቸው፡፡ “በጋራ እንችላለን” ብለው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን እውን አደረጉ፡፡ “በጋራ ኢትዮጵያን አረንጓዴ እናልብስ” ብለው ላለፉት ስድስት ዓመታት ከ40 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን…

የፕሬስ መግለጫ

ጉባኤዉ ኢትዮጵያ ልምድ ያካፈለችበት እና የመፍትሔ አካል ኾና የቀረበችበት ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ያስተናገደችዉ 2ኛዉ የዓለም የምግብ ሥርዐት ጉባኤ ልምድ ያካፈለችበት እና ለምግብ ሥርዐት መስተካከል መፍትሔዎችን ያቀረበችበት ነበር፡፡ የኢትዮጵያ እና የጣሊያን መንግሥታት ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጋር በመቀናጀት ያዘጋጁት የዓለም የምግብ ሥርዐት ጉባኤ በርካታ መሪዎች፣ የግብርናዉ ዘርፍ ተመራማሪ ግለሰቦች እና ተቋማት እንዲሁም ሌሎች የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በታደሙበት በአዲስ…

|

መንግሥት የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ዛሬም እንደ ትናንቱ በትጋት ይሠራል፡፡

የአማራ ክልል ሕዝብ ባለፉት ጥቂት ዓመታት መክፈል የማይገባዉን ውድ ዋጋ በጥቂት ጥቅመኞች ምክንያት እየከፈለ ይገኛል፡፡ የፋኖን ታሪካዊ አነሣሥ እና ዓላማ ባልተከተለ አግባብ ራሳቸዉን በፋኖ ስም የሚጠሩ ፅንፈኛ ኃይሎች በቀሰቀሱት ግጭት የአማራ ክልል ሰላም እና ልማት ክፉኛ ተጎድቷል፡፡ ፋኖ ሀገር በባዕድ ወራሪ እጅ በወደቀችበት እና ማእከላዊ መንግሥት በግዞት በቆየበት ወቅት ሀገርን ለማዳን የተደረገ ተጋድሎ የተመራበት ድንቅ…

ኢትዮጵያ ከሕዝቦቿ ጋር እየመከረች ተግዳሮቶችን በመሻገር ስኬቶቿን ታስቀጥላለች!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባለፉት ሳምንታት ከመላዉ ኢትዮጵያ ከተውጣጡ ከንግዱ ማኅበረሰብ፣ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፣ ከመምህራን ተወካዮች፣ የጤና ባለሙያዎች፣ የኪነ-ጥበብ ባለሞያዎች እንዲሁም የመገናኛ ብዙሃን ተወካዮች ጋር ሁሉን አቀፍ እና ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል። ውይይቶቹ በየዘርፉ ያሉ ፍላጎቶችንና ተግዳሮቶችን ለክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ፊት ለፊት ለማቅረብ እድል የፈጠሩ፣ ከዚህም አኳያ በአጭር ጊዜ ሊፈቱ የሚችሉ ጉዳዮች አቅጣጫ የተሰጠባቸው እና…

“የነገዋ ኢትዮጵያችን በአስተማማኝ መሠረት ላይ እንድትቆም ወሳኝ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮቿ ላይ እየመከረች ነው።”

ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያውያን የጋራ ዘርፈ ብዙ እና ውስብስብ የሆኑ ችግሮቻቸዉን በምክክር ለመፍታት ቆራጥ ርምጃ ወስደው የተነሡበት ወቅት ነው። ሀገራችን በበርካታ ጉዳዮች በተቃርኖዎች ውስጥ ለረዥም ዘመናት ስትናጥ እና በአስከፊ ግጭቶች ውስጥ ስታልፍ ቆይታለች። በተለይም ለረዥም ዓመታት እጅግ መሠረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በፖለቲካ እና በሐሳብ መሪዎች እንዲሁም በኅብረተሰቡ ክፍሎች መካከል ልዩነት እና አለመግባባቶች ኖረዋል። እነዚህን አለመግባባቶች…

ወቅታዊ መረጃ

ሃገራችን ኢትዮጵያ በያዝነው ሳምንት መጨረሻ የሚካሄደውን የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ ከወትሮው በላቀ መልኩ በድምቀት ለማስተናገድ አስፈላጊውን ሁሉ ቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ እንግዶቿን ለመቀበል ዝግጁ ሆናለች። ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ኅብረት ምስረታም ሆነ ከተመሰረተ በኋላ ከሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ጋር በመሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጋለች። የኅብረቱ መቀመጫ እንደመሆናችንም በየዓመቱ የሚካሄዱ የአስፈጻሚዎች እና የመሪዎች ስብሰባዎችን በድምቀት ስናስተናግድ ቆይተናል። የአፍሪካ ኅብረት ሃገራችን ኢትዮጵያ ለፓን…