ኢትዮጵያ እየተከለች ነው፡፡

በሐረር ከተማ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ተገንብቶ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘውን የሐረሪ ክልል ባህል ማዕከልን የጋዜጠኞችና የኮሙኒኬሸን ባለሙያዎች ቡድን ዛሬ ጎብኝቷል፡፡ የባህል ማዕከሉ የወጣቶችን ስብዕና ለመገንባት እንዲሁም ስለ ሃገራቸውና ስለ ሃረሪ ክልል ባህላዊና ታሪካዊ እሴቶች ለማስተዋወቅ ያስችላል ተብሏል። ሐረር የመቻቻልና የፍቅር ከተማ መሆንዋን በተጨባጭ ለማሳየትና የቱሪዝም ማዕከልነቷን ለማሳደግ የባህል ማዕከሉ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የሐረሪ…
መላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለጳጉሜ 5 የነገ ቀን እና ለአዲሱ ዓመት ዋዜማ በሠላም አደረሳችሁ! ነገ የጊዜ መቍጠሪያ ብቻ አይደለም፤ ነገ ተስፋ፣ ምኞት፣ ስንቅ፣ ለዛሬ መነሣሣትና ትጋት ምክንያት ጭምር ነው፡፡ ነገ ሁላችንም ለማየት የምንጓጓለት፣ የተሻለ ሕይወትና ስኬት እንዲኖረን የምንመኘዉ መሻታችን ነው፡፡ እንደግለሰብ የተሻለ ነገን እንመኛለን፤ እንደቤተሰብ የተሻለና የጋራ ደስታና ተድላ ያለው ነገን እናልማለን፤ እንደሀገር ሰላም፣ ደስታ፣ ብልጽግና…
<< ነሐሴ 17፣ 2016 ዓ.ም በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ዓሻራችንን እናኑር::በአንድ መንፈስ በመላው ኢትዮጵያ ዓሻራችንን እናኑር፡፡ አንድ ከሆን ከዚህም በላይ እንችላለን!አዋቂዎች ከ20 በላይ፣ ታዳጊወች ከ10 በላይ በመትከል ለሀገር ያለንን ፍቅር፣ ለትውልድ ያለንን ስጦታ በተገቢው ስፍራ እንግለጥ፡፡Hagayya 17/2016 guyyaa tokkotti biqilruuwwan miliyoona 600 dhaabuudhaan ashaaraa keenya haa keewwannu.Guutummaa Itoophiyaatti qalbii tokkoon ashaaraa keenya haa…
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና በህዝቡ ትብብር እየተገነቡ ያሉ የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ተቋማት የሕብረተሰቡን ተሳትፎ በእጅጉ ሊያሳድጉ የሚችሉ መሆናቸው ተገለጸ፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን ያዘጋጁት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ቡድን ጉብኝት በሁለተኛ ቀን ቆይታው በድሬዳዋ እየተከናወኑ ያሉ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውሮ ተመልክቷል። በዛሬው እለት የድሬዳዋ የወጣቶች ስፖርት አካዳሚ፣ የድሬዳዋ ስታዲየም ማሻሻያ ፕሮጀክት፣ የድሬዳዋ…
መገናኛ ብዙሃን በግብርናው ዘርፍ የተገኙ ውጤቶችንና አዳዲስ የምርምር ስራዎችን በተገቢው መልኩ ለሕብረተሰቡ ተደራሽ ሊያደርጉ እንደሚገባ ተገለጸ። መንግስት የሃገሪቱን ሰላምና ደህንነት ከማረጋገጥ ጎን ለጎን ትልቁ ትኩረቱ ምርታማነትን ማሳደግ በመሆኑ ሕብረተሰቡ ሙሉ ትኩረቱን ወደ ልማት እንዲመልስ ለማድረግ የመገናኛ ብዙሃን የበኩላቸውን ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ ተናገሩ፡፡ ዛሬ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ከፍተኛ አመራሮችና…