ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ ትስስርን የበለጠ ለማጎልበት፣

ንግድን ለማቀላጠፍና ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለመደገፍ የመንገድ አውታሯን በንቃት እያስፋፋችና እያሻሻለች ትገኛለች።

አሁን ላይ እየተከናወኑ ያሉ ጥረቶች ትኩረት የሚያደርጉት አዳዲስ አውራ ጎዳናዎችን እንዲሁም የገጠር እና የከተማ መንገዶችን በመገንባት በተጨማሪም ነባር መንገዶችን በማዘመን የጉዞ ጊዜን ለማሰጠር፣ ደህንነትን ለማሻሻልና የትራንስፖርት ወጪን ለመቀነስ ነው።

እነዚህ ተግባራት የትምህርት፣ የጤና፣ የገበያ አገልግሎቶችን ተደራሽነት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ከማሳደጋቸውም በላይ ለኢንዱስትሪ፣ ለግብርና እና ለአካባቢው ንግዶች መሳለጥ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ።

ኢትዮጵያ ለግንባታም ሆነ ለጥገና ስራዎች ቅድሚያ በመስጠት፣ ቀጠናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች የዕለት ተዕለት ኑሮን በማሻሻል፥ ይበልጥ ቀልጣፋ፣ አስተማማኝና ቀጣይነት ያለው የመንገድ ስርዓት እውን እያደረገች ነው።

PMOEthiopia

VisionOfProsperity

የኢትዮጵያብልጽግናራእይ

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

Similar Posts