በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውና ከዳር እስከ ዳር ኢትዮጵያውያንን በጠረጴዛ ዙሪያ የሚያሰባስበው ታሪካዊው ሀገራዊ የምክክር መድረክ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ይጀምራል።
ይህ አዲስና ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ለአሁኑም ሆነ ለሚመጣው ትውልድ የምስራች ነው። ኢትዮጵያ በጦርነት የተመሰረተች ሀገር ሳትሆን በሕዝቧ መግባባት እና በጋራ ትርክት ላይ የምትገነባ መሆኗን የሚያረጋግጥ ወሳኝ የሀገር ግንባታ ሂደት ጭምር ነው።


