አዲስ ስፖርት ፓርክ፤ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የስፖርትና የውበት አሻራ።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
ለዜጎቻችን ጤና እና ለከተማችን ዕድገት ያለንን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጠው ይህ ስራ፤ ከፕሮጀክት የተሻገረ፣ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ እውነተኛ ገጽታ ነው! ለሁሉም ዜጋ የተገነባው ይህ ማዕከል የሚከተሉትን አካቷል፦ • 5.7 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የስፖርት እና የአረንጓዴ መዝናኛ ስፍራ፤ • የቀጣዩን ትውልድ ለማነቃቃት በኦሎምፒክ መድረክ ለሀገራችን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኙ የ15 አትሌቶቻችን የክብር ሐውልቶች፤ •…
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና በህዝቡ ትብብር እየተገነቡ ያሉ የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ተቋማት የሕብረተሰቡን ተሳትፎ በእጅጉ ሊያሳድጉ የሚችሉ መሆናቸው ተገለጸ፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን ያዘጋጁት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ቡድን ጉብኝት በሁለተኛ ቀን ቆይታው በድሬዳዋ እየተከናወኑ ያሉ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውሮ ተመልክቷል። በዛሬው እለት የድሬዳዋ የወጣቶች ስፖርት አካዳሚ፣ የድሬዳዋ ስታዲየም ማሻሻያ ፕሮጀክት፣ የድሬዳዋ…
ወ/ሮ ሃና ተህልኩ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ #PMOEthiopia Post Views: 32
ውድ ኢትዮጵያዊያን በዚህ ሳምንት ውዷ ሀገራችን በአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ለመታደም የሚመጡ እህት ወንድም አፍሪካዊያንን ለመቀበል ልቧን ከፍታ-እጆቿን ዘርግታ ትቀበላለች። እነዚህ ወዳጆቻችን የሰንደቃችንን ቀለማት የሚጋሩ፣ ኢትዮጵያን እንደነፃነት ቀንዲል የሚመለከቱ ብሎም ሀገራችን የአኅጉሩ የፖለቲካ ርዕይ የማዕዘን ድንጋይ አድርገው የሚያከብሩ ናቸው። ኢትዮጵያ ወደር በሌለው እንግዳ ተቀባይነቱ ለምን ልትከበር እንደበቃች በአቀባበላችን እናሳያቸው። እንደቤታቸው እንዲሰማቸው እናድርግ። በክብር እንቀበላቸው። በፍቅር እናቆያቸው።…
ኢትዮጵያን ወደ ነበራት ጥንታዊ የደን ሽፋን በመመለስ አረንጓዴ ካባ ለማልበስ የጀመርነው ጥረት 7ኛ ዓመቱ ላይ ደርሷል፤ 7ኛ ዓመት የጥረታችንን ጅማሮ የምንዘክረዉ ደግሞ በአንድ ጀምበር 700 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ነው፡፡ ባለፉት 6 ዓመታት የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዟችን ኢትዮጵያውያን ከሁሉም አቅጣጫ፣ ከደጋ እስከ ቆላ በጋራ ባደረግነዉ ጥረት 40 ቢሊዮን ችግኞች በላይ ተክለናል፤ የኢትዮጵያን የደን ሽፋንም እስከ ባለፈዉ ዓመት…
ምክር ቤቱ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች፡- 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ነው፡፡ ኮሚሽኑ ሀገራችን የኒውክለር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ መንገድ ከዓለም አቀፍ ማዕቀፎች ጋር በተጣጣመ መልኩ በኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት፣ በኢንዱስትሪ ልማት፣ በምግብ ዋስትና፣ በጤና አገልግሎት፣ በሳይንስ እና ምርምር ዘርፎች ላይ ለመጠቀም የምታደርገውን ጥረት የመምራትና…