አዲስ ስፖርት ፓርክ፤ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የስፖርትና የውበት አሻራ።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
PMOEthiopia Post Views: 81
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያዊነትን የገለጹበት መንገድ የመደመር ፍልስፍና መሠረት ሲሆን ኢትዮጵያዊነትን በአንድ ወገን ወይም በአንድ ቀለም ሳይሆን፣ በሁለንተናዊ የኅብረት ስብስብ መልክ አስቀምጠዋል። “ኢትዮጵያዊነት በኅብር ቀለም የሚሳል፤ በኅብር ባህል ሚኖር፤ በኅብር ቋንቋ የሚነገር፤ በኅብር ደም የተሠራ፤ በኅብር ላብ የሚገነባ፤ በኅብር ጥበብ የሚሻገር” የሚለው ሐሳብ፣ ብዝኃነትን እንደ ስጋት ሳይሆን እንደ ጥሬ ኃይል (Raw Power) ያሳያል። እያንዳንዱ…
በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የተናበበና የተቀናጀ መረጃ ከተቋማት ጋር የመለዋወጥ ዐቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ መሻሻል እያመጣ እና ውጤት እየተመዘገበ መሆኑንና ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎቱ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ አስታውቀዋል። የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የፌዴራል እና የተጠሪ ተቋማት የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራዎች የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ የጋራ መድረክ በአዳማ እየተካሄደ ነው።…
ማንኛዋም ሴት ከህልሟ እንዳትደርስ፤ ያሰበችውን ሰርታ እንዳታሳካ እንቅፋት የሚሆኑባትን ፆታዊ ጥቃቶች ማስቆም የሁላችንም ኃፊነት ሊሆን ይገባል ሲሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ ሰላማዊት ካሳ ተናገሩ፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሰራተኞችና አመራሮች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በአዲስ አበባ ሴቶች ማህበር በተመሰረተው ፆታዊ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች መቆያና መልሶ ማቋቋሚያ ማእከል ተገኝተው ድጋፍ በማድረግ በጋራ አክብረዋል። አገልግሎቱ የንፅህና መጠበቂያና…
ዛሬ ወደ የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር አ.ማ ጉብኝት አድርገናል። ጉብኝቱ የሀገራችንን ብሔራዊ የሎጂስቲክስ ክዋኔ ዐቅም ለመገምገም እና የሀገሪቱን እያደገ ያለ የልማት አጀንዳ ለመደገፍ በሎጂስቲክስ ዝግጁነት ላይ ገንቢ ውይይቶችን ለማካሄድ ጠቃሚ ዕድል ሰጥቶናል። ኢኮኖሚያችን እያደገ ሲሄድ የሎጂስቲክስ ዘርፉ ካልዘመነ ዘላቂ ዕድገትን የሚገድብ ዋና መሰናክል መሆኑን ይቀጥላል። አሁን በተለይ በውስጣዊ እና በራስ ዐቅም የባቡር መንገድ ግንባታ ላይ…
ዛሬ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ የተመረቀው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት ከያዛቸው መሰረተ ልማቶች ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፤ - የወንዝ ልማት፦ 1 ትልቅ ግድብ፣ 16 አነስተኛ ግድቦች፣ 3 ቼክ ዳሞች እና 20.2 ኪ.ሜ የድጋፍ ግንብ። - የወንዝ ዳርቻ ልማት፦ 36,928 ካ.ሜ የአፈር እና ስነ-ምህዳር ጥበቃ ስራዎች (የኮንሶ ጋቢዮን እና እርከን)። - አረንጓዴ ልማት፦ 59.7 ሄክታር…