የህዳሴ ግድብ በተርባይን ከሚያልፈው ውሃ በተጨማሪ በግድቡ ውሃ ማስተንፈሻ በሮች / Spillway/ በአንድ ሰከንድ 2800 ሜትር ኪዮብ ውሃ ወደ ተፋሰስ ሀገራት መልቀቅ ጀምራል።


ሃገራዊ ለውጡ ለኢኮኖሚው ስርዓት ካስተዋወቃቸው ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን አንዱ ነው። ይህ ባለስልጣን የካፒታል ገበያ ስርዓትን ፈጠራን በማበረታታት በካፒታል ፈላጊዎች እና ካፒታል አቅራቢዎች መካከል ድልድይ የሚሆን ስርዓት እየገነባ ነው። በኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም በሃገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቀው የካፒታል ገበያ ስርዓት ባለፉት ዓመታት የተለያዩ ሂደቶችን አልፎ ሶስት ቁልፍ ተቋማትን መፍጠር ተችሏል። እነዚህም…
የኢትዮጵያ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ብሔራዊ ስትራቴጂን በተመለከተ በሰፈረመቅድም፣ ፕሮጀክቱ ከዲጂታል ዘመን አደጋዎችና ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ልማትና ሉዓላዊነትን በማጎልበት የኢትዮጵያን የልማት ጎዳና በራሱ ለመቅረጽ ቁርጠኛ መሆኗን ቀጥላለች። “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ፣ በዓላማ፣ በቁርጠኝነትና በችሎታ ላይ የተመሠረተ ብሔራዊ ምላሽ መስጠት ነው:: ስትራቴጂው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2030 ታላቅ ልማትን ለማስመዝገብ ያለውን ከፍተኛ ምኞት የሚያሳይ ሲሆን፣ በኢኮኖሚ፣ በመንግሥታዊ አስተዳደርና በማኅበራዊ ዘርፎች…
ክቡር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን፣ በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር እንዲሁም በደሴ እና ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደሮች ተገኝተው የተከናወኑ የልማትና የኮሙኒኬሽን ተግባራትን ምልከታ አድርገዋል:: በጉብኝቱ ወቅት በዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች ዘላቂ ሰላምን ለማጽናት የተሰሩ ስራዎች ለሌሎች አካባቢዎች በተምሳሌትነት የሚወሰዱ መሆናቸው ገልጸው…
ሀገር በቀል የምጣኔ ኃብት ማሻሻያ ሥራዎችአንደኛ በመንግሥት እጅ የነበሩትን የልማት ተቋማት ወደ ግሉ ዘርፍ ማስተላለፍ (Privatization)፣ ሁለተኛ የንግድ አሠራር ማሻሻያ (Ease of doing business) ሦስተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረትና የውጭ እዳ አከፋፈል ችግሮችን ለመፍታት የተሰሩ ማሻሻያዎች ናቸው።የግሉን ዘርፍ ከመንግሥት ጋር በጋራ ለማሳተፍ በወጣው አዋጅ የግሉ ዘርፍ እንዴት ተሳትፎ ማድረግ እንደሚችል መንግሥት ዝርዝር መረጃ ሰጥቷል። ትውልደ ኢትዮጵያውያን…
ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ ዛሬ ሐምሌ 29 ቀን 2015 ዓ.ም በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በክልሉ ያለው የጸጥታ ሁኔታ በመደበኛ የሕግ ማስከበር ስርአት መቆጣጠር እንደማይቻል በመግለጽ ለፌዴራል መንግስት ጥያቄ ማቅረቡን አስታውሰዋል፡፡ ይህን ተከትሎ መንግሥት ሰላምን፣ የሃገር ደህንነትን እንዲሁም ሕገ መንግስታዊ ስርአትን የማስከበር ኃላፊነት ያለበት በመሆኑ በክልሉ የሚታየውን ሕገ ወጥ…