Similar Posts
የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን እና የኢትዮጵያዊያንን ዉበት የሚያጎላ ነው፡
ኢትዮጵያ የብዝኃ ቋንቋ፣ ብዝኃ ባህልና ብዝኃ ማንነት ሃገር ናት፡፡ ብዝኃነት ለኢትዮጵያዊያን ተፈጥሯችን፣ ዉበታችንና የጥንካሬአችን ምንጭ ነው፡፡ ብዝኃ ማንነት ያለበት ሕዝቦች ሀገር መሆናችን ጸጋችን ነው፤ ብዝኃነት የኢትዮጵያ ተጨባጭ እዉነታና ውብትም ነው፡፡ በኢትዮጵያ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ሂደት አንድ ጠንካራ ሀገር ለመገንባት በርካታ መንገዶች ተሞክሯል፡፡ ነባሩንና ተፈጥሯችን የሆነውን ብዝኃ ማንነትን በአንድ ወጥ ማንነት ለመቀየር ብዙ ተለፍቶበታል፡፡ በፖሊሲና ተቋማዊ አሰራር…
ኢትዮጵያዊነት በኅብር ቀለም!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያዊነትን የገለጹበት መንገድ የመደመር ፍልስፍና መሠረት ሲሆን ኢትዮጵያዊነትን በአንድ ወገን ወይም በአንድ ቀለም ሳይሆን፣ በሁለንተናዊ የኅብረት ስብስብ መልክ አስቀምጠዋል። “ኢትዮጵያዊነት በኅብር ቀለም የሚሳል፤ በኅብር ባህል ሚኖር፤ በኅብር ቋንቋ የሚነገር፤ በኅብር ደም የተሠራ፤ በኅብር ላብ የሚገነባ፤ በኅብር ጥበብ የሚሻገር” የሚለው ሐሳብ፣ ብዝኃነትን እንደ ስጋት ሳይሆን እንደ ጥሬ ኃይል (Raw Power) ያሳያል። እያንዳንዱ…
ሚዲያዎች የአካባቢ ጥበቃ ስራ የሁሉም ዜጎች የእለት ከእለት ልምምድ የሚጠይቅ መሆኑን በመረዳት ቀጣይነት ያላቸው እና ለውጥ የሚያመጡ የግንዛቤ ማስጨበጫ ይዘቶችን መስራት ይጠበቃል።
አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ የኢፌዲሪ መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት በጋራ በመተባበር የሁለተኛው ዙር የፅዱ ኢትዮጵያ ንቅናቄን መሰረታዊ አላማና ግቦችን፤ እንዲሁም በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ላይ ለሚዲያ ባለሙያዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥተዋል። አካባቢን ለመጠበቅ እና ጽዱ ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የሚዲያ ባለሞያዎች ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር ከፍተኛ ሀላፊነት ያለባቸው መሆኑን ገልፀው…
“ኢትዮጵያ ለሁለንተናዊ ጉዳዮች ጥንቃቄ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ትገኛለች።
“ኢትዮጵያ ለሁለንተናዊ ጉዳዮች ጥንቃቄ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ትገኛለች። በሚዲያ ሥራ ጥረቶቻችን የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም፣ ሰላም እና ፍቅር ቅድሚያ ሰጥተን መሥራት ይገባናል። ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር ምን ጠቃሚ ሥራ እየሠራን ነው ብለን ራሳችንን ሳናሰልስ መጠየቅ አለብን። በዛሬው ዕለት ሀገራዊ ልማት እና ኅብረትን በማስተዋወቅ ብሎም ብሔራዊ ጥቅምን በማስጠበቅ ጥረት ረገድ ከፍ ያለ ሥራ በመሥራት ሽልማት ለተበረከተላቸው የሚዲያ ተቋማት…
“እንደ ሃገር የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ትርጉም ባለው የኮሙኒኬሽን ስራ መደገፍ ይገባቸዋል፡፡”
ክቡር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን፣ በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር እንዲሁም በደሴ እና ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደሮች ተገኝተው የተከናወኑ የልማትና የኮሙኒኬሽን ተግባራትን ምልከታ አድርገዋል:: በጉብኝቱ ወቅት በዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች ዘላቂ ሰላምን ለማጽናት የተሰሩ ስራዎች ለሌሎች አካባቢዎች በተምሳሌትነት የሚወሰዱ መሆናቸው ገልጸው…
“የመገናኛ ብዙኃን የተረጂነት አስተሳሰብን በመለወጥ ዜጎች ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል ተረጂነት ሃገራዊ ክብርንም የሚነካ መሆኑን በማስረዳትና ግንዛቤ በመፍጠር በኩል ከፍተኛ ኃላፊነት ተጥሎባችኋል፡፡”
ሰላማዊት ካሳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ከኢትዮጵያ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ጋር በመተባበር የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ፖሊሲ ላይ ለሁለት ቀናት የተዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ ሚኒስትር ዴኤታዋ እንዳሉት የሰብአዊ ድጋፍ ጠባቂነት አመለካከትን መየቀር የመገናኛ ብዙኃንና የኮሙኒኬሽን ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ኃላፊነት ነው፡፡ ኢትዮጵያ ትልቅ አቅም፣ሐብት ያላት ሃገር ናት ያሉት ሰላማዊት ካሳ…
