የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

“የአውሮፓ ሕብረት የውጭ ጉዳይና የደህንነት ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይ የተከበሩ ካያ ካላስን ዛሬ ተቀብዬ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።

‎በአውሮፓ ሕብረት እና በአፍሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ማጠናከር ላይ የመከርን ሲሆን በጋራ ጥቅሞች እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሃሳብ ተለዋውጠናል።
‎በተጨማሪም ትኩረት የሚሹና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መሰረት ባደረገው ውይይታችን፤ ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ይበልጥ ለማሳደግና ለማስፋፋት በሚያስችሉ መንገዶች ላይ መክረናል።”

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

Similar Posts