ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ ተጠናቋል

“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ ተጠናቋል። በዛሬው እለትም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ አስጀምረናል። ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች ናቸው። እነዚህ ትልሞች እንዲሳኩም በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማት ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ የሚከናወን ሲሆን፣ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ቅድሚያ በሚሹ እና በቀጠናው መረጋጋት በሚፈጥሩ የልማት አጀንዳዎች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድን ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ተቀብያለሁ

“የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድን ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ተቀብያለሁ። ባለፈው አንድ አመት እየሰራንባቸው የቆየነውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ውይይቶች በመቀጠል ፍሬያማ ውይይት አድርገናል። የሃሳብ ልውውጣችን የወል የቅድሚያ ጉዳዮቻችንን ለመከወን ብሎም ለጠንካራ ግንኙነት፣ ቀጠናዊ መረጋጋት እና ልማት ያለንን ቁርጠኝነት በድጋሚ ያፀና ነበር።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

የመደመር እሳቤ ከሥልጣኔ አድማስ እስከ ኢኮኖሚያዊ ፍትሐዊነት፣

የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የመደመር እሳቤ (Synergy) በሕንድ የታወቀ መሆኑን መግለጻቸው፣ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፍልስፍና አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነትን የሚያሳይ ሲሆን ይህ እሳቤ ከጥንታዊ ሥልጣኔ ዕሴቶች ተነስቶ እስከ ዘመናዊ የኢኮኖሚ አስተዳደር ድረስ ያለውን ጉዞ መተንተን ይቻላል። ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ለእያንዳንዱ ሀገር ዕድገት እርስ በእርስ መተማመንና በጋራ ጥረት በአብሮነት መጓዝ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሐሳብ የመደመር…

“ልክ እንደ ሕንድ፣ እራሳችንን ከውስጥ በማጠናከር እና ከአለም ጋር በመተሳሰር እናምናለን።”

“ልክ እንደ ሕንድ፣ እራሳችንን ከውስጥ በማጠናከር እና ከአለም ጋር በመተሳሰር እናምናለን።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

ከጉጃራት መንገዶች እስከ አዲስ አበባ ቤተ-መንግስት፤ የስብዕና እና የዲፕሎማሲ ጥበብ፣

የህንድ 15ኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ በአዲስ አበባ ያደረጉት ጉብኝት፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሺህ ዓመታት ድልድይ ዳግም ያደሰ ክስተት ሆኖ ተመዝግቧል። ናሬንድራ ሞዲ ህንድ ነፃ ከወጣች በኋላ ተወልደው ሀገሪቱን ለመምራት የበቁ የመጀመሪያው መሪ ሲሆኑ የወጣትነት ዘመናቸውን ለአጭር ጊዜ እንደ መነኩሴ ከሀገር ሀገር በመዘዋወር ያሳለፉት ሞዲ፣ ዛሬም ድረስ ያ መንፈሳዊ ጽናት አብሯቸው ይገኛል። ከፖለቲካው ጀርባ…

የፀና ዲፕሎሲያዊ ልህቀት በሉአላዊት ኢትዮጵያ

የፀና ዲፕሎሲያዊ ልህቀት በሉአላዊት ኢትዮጵያ ታኅሣሥ 8/ 2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከዓለም ጥንታዊት ሀገር የላቀ ክብር የሰጡኝ ታላቅ የኒሻን ክብር፣ ከኢትዮጵያ ህዝብ የተበረከተልኝ እዉቅናና ሽልማት እንደሆነ እገነዘባለሁ፡፡ ይህንን የክብር እዉቅናና ስጦታ በብዙ ሰብአዊነት እና የሕንድ ህዝብ ምስጋና አድርጌ እቀበላለሁ፡፡ ሽልማቱም የተሰጠዉ የሁለቱን ወዳጃዊ አጋርነታችንን የቀረጹ እና ትልቅ ድርሻ ላበረከቱ ስፍር ቁጥር ለሌላቸው ሕንዳውያን…

ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ህብረት አፍሪካን በሚገባ የሚወክል ኮፕ 32 ለማዘጋጀት እንዴት ተቀራርበው መስራት እንደሚችሉ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር እና ከቡድናቸው ጋር ውይይት አድርገዋል

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ህብረት አፍሪካን በሚገባ የሚወክል ኮፕ 32 ለማዘጋጀት እንዴት ተቀራርበው መስራት እንደሚችሉ ከአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር እና ከቡድናቸው ጋር ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸውም በክቡር ማህሙድ አሊ የሱፍ መሪነት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን COP32ን የተሳካ ለማድረግ የኢትዮጵያ ቁልፍ አጋር ለመሆን ቁርጠኛ መሆናቸውን መግለጻቸውን አስታውቀዋል።

የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የኢትዮጵያ ጉብኝት እና አንድምታዉ

“ከአንበሶች ግዛት እስከ አንበሶች ምድር” የጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ታሪካዊ የፓርላማ ንግግር” ኢትዮጵያና ሕንድ እንደ ሀገር ግንኙነት ከመሰረቱበት ጊዜ ጀምሮ በንግድ፣ በልማት እና በባህል ልውውጥ ዘርፎች ላይ በመተባበር ጥብቅ ወዳጃዊ ግንኙነት ሲያደርጉ ቆይተዋል። ሁለቱ ሀገራት የአየር ንብረት ለውጥን እና የደህንነት ጉዳዮችን ጨምሮ በአለም አቀፍ መድረኮች ላይ አንዳቸው የሌላውን ጥቅም ሲደግፉም ቆይተዋል። በኢትዮጵያና በሕንድ መካከል እየዳበረ የመጣው…

ኢትዮጵያዊያን ለሰላም፣ ለልማትና ዲሞክራሲ በአንድነት የሚነሱበት ትክክለኛ የከፍታ ጊዜ አሁን ነዉ – የሕንድ ሪፓብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ

ታኅሳስ 8/2018 ዓ.ም ኢትዮጵያዊያን ለሰላም፣ ለልማትና ዲሞክራሲ በአንድነት የሚነሱበት ትክክለኛ የከፍታ ጊዜ አሁን ነዉ – የሕንድ ሪፓብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ታኅሳስ 8/2018 ዓ.ም የሕንድ ሪብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ለሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች አባላት ሰፋ ያለ ንግግር አድርገዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ባደረጉት ንግግር፣ ጊዜዉ ትክክለኛ የኢትዮጵያ ከፍታ በመሆኑ ኢትዮጵያዊያን ለሰላም፣ ለልማትና…