የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልክተኛ ክቡር ቺፍ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ በሀገራዊ ምክክር ያስተላለፉት መልእክት

የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት እና የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልክተኛ ክቡር ቺፍ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ በሀገራዊ ምክክር ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያን ታሪክ፣ የህዝቦቿን ብዝሃነትና ታታሪነት በመጥቀስ ይህ ህዝብ የሰነቀውን ብሩህ ተስፋ ለማሳካት ደግሞ አሁን የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ስኬት ቁልፍ መሆኑን አብራርተዋል። PMOEthiopia ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮችhttps://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

የኢጋድ ዋና ፀሐፊ ክቡር ወርቅነህ ገበየሁ በሀገራዊ ምክክር መክፈቻ ሥነ ስርዓት ላይ ያስተላለፉት መልእክት

ባስተላለፉት መልዕክት፤ በዓለም ታሪክ ውስጥ በግጭት የተገነባ ወይም ያተረፈ ሀገር አለመኖሩን አስገንዝበዋል። አክለውም በፖለቲካ ባህል ውስጥ ልዩነቶች መኖራቸው ተፈጥሮአዊ ቢሆንም፤ ትልቁና መሰረታዊው ስህተት ግን እነዚህን ልዩነቶች በኃይል ለመፍታት መሞከር እንደሆነ ነው ያነሱት። ከሁሉ በላይ ልዩነቶችን መፍታት የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ፣ በመነጋገርና በተለያዩ ሰላማዊ መድረኮች መሆኑን ያብራሩት ዋና ፀሐፊው፤ ኢትዮጵያም ለዚህ የሚሆኑ በርካታ ባህላዊ የምክክር መንገዶች ያሏት…

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአራት ዓመታት ጉዞ ኤግዚቢሽን ተጎበኘ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አመራሮች ጋር በመሆን፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑን የአራት ዓመታት ጉዞ የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ጎብኝተዋል። #PMOEthiopia

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውና ከዳር እስከ ዳር ኢትዮጵያውያንን በጠረጴዛ ዙሪያ የሚያሰባስበው ታሪካዊው ሀገራዊ የምክክር መድረክ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ይጀምራል።

‎ይህ አዲስና ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ለአሁኑም ሆነ ለሚመጣው ትውልድ የምስራች ነው። ኢትዮጵያ በጦርነት የተመሰረተች ሀገር ሳትሆን በሕዝቧ መግባባት እና በጋራ ትርክት ላይ የምትገነባ መሆኗን የሚያረጋግጥ ወሳኝ የሀገር ግንባታ ሂደት ጭምር ነው።

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

“ዛሬ በታሪካዊው የሀገራዊ ምክክራችን ዋዜማ፣ የኢትዮጵያ ታላቅ ወዳጅ የሆኑትን ክቡር ኦሊሴጉን ኦባሳንጆን በጽሕፈት ቤቴ ተቀብያለሁ። በመጪው ሀገራዊ ምክክር ዙሪያ ለመወያየት እንዲሁም ከዚህ ቀደም ካከናወኗቸው ተግባራት ጥበብ ለመቅሰም ችለናል፤ በተለይም የቢያፍራን የሰላም ሂደት በመምራት ያካበቱትን ልምድ አጋርተውናል። ይህም ኢትዮጵያ በምክክር ለምታረጋግጠው አንድነትና ዘላቂ የሰላም ጉዞ ላይ ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለምታበረክቱት በዋጋ የማይተመን አስተዋጽኦ ሁልጊዜም…

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

“ኢትዮጵያ ለታሪካዊውና ታላቁ የሀገራዊ ምክክር በምትሰናዳበት በዚህ ወሳኝ ታሪካዊ ወቅት፤ ለመላው የሀገሬ ልጆች የማስተላልፈው ታላቅና የከበረ ጥሪ አለኝ። ነገ የሚጀመረው ውይይት ፍቱን የፖለቲካ መድረክ ብቻ ሳይሆን፣ የእኛን እና የመጪውን ትውልድ እጣ ፈንታና የወደፊት ተስፋ ሙሉ በሙሉ የሚወስን አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ጭምር ነው። ‎ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣ መረጋጋትና ሁለንተናዊ ብልጽግና የምትተጉ፣ የኢትዮጵያ ታላቅነት ግድ የሚላችሁ ሁሉ፤ ፈረሱም…

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

“የቤኒን ፕሬዝዳንት ክቡር ሮሙዋልድ ዋዳግኒን ‎ተቀብዬ በወል ጉዳዮች ዙሪያ መክረናል። ‎የሁለትዮሽ ግንኙነታችን መጠናከር እና በጋራ ጥቅሞች ላይ የላቀ ትብብር ለማድረግ በሚያስችሉ እድሎች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል። ለጥልቅ አጋርነት እና ለዘላቂ ወዳጅነት ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት ይበልጥ እንደምናሳድግ ጽኑ ፍላጎት አለን።”