ዛሬ ማለዳ በባሌ ዞን፣ ደሎ መና ወረዳ በመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አማካኝነት የተጀመረውን የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክትን መርቀናል። ፕሮጀክቱ የወልመል ወንዝን በመስኖ በሚገባ በመጠቀም የግብርና ምርታማነትን በማላቅ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተከናወነ ነው። ፕሮጀክቱ ዘላቂ የገጸምድር የመስኖ ሥርዓት በመገንባት የግብርና ስራው ለዘመናት በዝናብ ውሃ ላይ ተመስርቶ የነበረውን የአካባቢውን ሕዝብ ዘላቂ የኑሮ ዘዴ ለማጎናፀፍ ታልሞ ተከናውኗል።

ፕሮጀክቱ በሙሉ አቅሙ ወደ ተግባር በሚገባበት ወቅት 20,000 ለሚሆኑ አርሶአደሮች ለሚያገለግል 9687.45 ሄክታር የእርሻ መሬት አስተማማኝ የመስኖ አቅርቦት ይኖረዋል። ይኽም የግብርና ምርታማነትን የሚያሳደግ፣ ለድርቅ የማይበገር ከባቢን የሚፈጥር ብሎም በማኅበረሰቡ አዳዲስ የሥራ እድል የሚፈጥር ይሆናል። ከነዚህ ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ባሻገር የአካባቢውን የውሃ አስተዳደር ተቋማትን በማጠናከር፣ የአካባቢውን ሕዝብ ባለቤትነት በማሳደግ ብሎም የወልወልን ወንዝ ዘላቂ አጠቃቀም በማጎልበት የተሻለ የምግብ…

የባሌ ዞን የመጀመሪያ ቀን ጉብኝት ያሳየን በድንቅ ተፈጥሮ እና በልማት ሥራ እድገት መካከል ያለውን መስተጋብር ነው።

በአስደናቂ ብዝኅ መልኩ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የቱሪዝማችን አንዱ የማዕዘን ድንጋይ ሆኖ ቀጥሏል። ይኽ እምቅ አቅም በፓርኩ እምብርት ላይ የተገነባው የዲንሾ ሎጅ በቅርቡ ሲጠናቀቅ የበለጠ ይጠናከራል። በአቅራቢያው በመገንባት ላይ ያለውና በቅርቡ የሚጠናቀቀው የሶፍኡመር ሎጅ ቱሪዝምን የኢኮኖሚያችን ቁልፍ መሪ አድርጎ ያስቀመጠው የኢትዮጵያን የ10 አመት ስትራቴጂክ እቅድ የሚተገብር ነው። ሎጁ በሶፍኡመር ዋሻ የጎብኝዎችን ቆይታ ከፍ የሚያደርጉ እና…

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተጀመረው የፍትህ አሰጣጥ ቴክኖሎጂ በሁሉም ክልሎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ ።

ዛሬ በናይሮቢ፣ ኬንያ “ዲጂታላይዜሽንን ለቀጠናዊ የእሴት ሰንሰለት መጎልበት በመጠቀም ለዘላቂ እና አካታች እድገት ማዋል” በሚል ጭብጥ በተካሄደው 24ኛው የCOMESA መሪዎች ጉባኤ ላይ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን የአፍሪካን የኢኮኖሚ ታሪክ የመቀየር ልዩ እድል እንዳቀረበልን አፅንኦት ሰጥቼ አንስቻለሁ። እንደ አኅጉር የየሀገሮቻችንን ጥረቶች ለማጣመር እና ቀጠናዊ ትስስሮችን ለማፋጠን ክሂሎቱ እና መሠረቱ አለን።

በኢትዮጵያ ዲጂታል ክህሎትን ለማበልጸግ እና አስፈላጊ መሠረተ ልማት ለመገንባት ጥሩ ርምጃዎች ተራምደናል። የጋራ ዲጂታል ነጋችንን ለማሳደግ በትብብር ለመሥራት ዝግጁ ነን። Yaa’ii Hoogantootaa COMESA 24fa har’a Naayiroobii, Keeniyaatti yaada ijoo “Dijitaalaayizeeshinii hidhata sona naannawaa gabbisuuf fayyadamuudhaan misooma waaraafi haammataaf oolchuu” jedhuun taa’ame irratti, tiraanisfoormeeshiniin dijitaalaa seenaa dinagdee Afrikaa jijjiiruuf carraa addaa akka nuuf fide cimsee kaaseera….

ቴክኖሎጂን ለኢትዮጵያ ልማት በማዋል ረገድ ትብብር እና የፈጠራ ስራዎች ወሳኝ ሚና እንዳላቸዉ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ

ቴክኖሎጂን ለኢትዮጵያ ልማት በማዋል ረገድ ትብብር እና የፈጠራ ስራዎች ወሳኝ ሚና እንዳላቸዉ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ገለጹ

የኢፌድሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ቴክኖሎጂን ለኢትዮጵያ ሁሉ አቀፍ ልማት በማዋል ረገድ የላቀ ትብብር እና የፈጠራ ስራዎች ወሳኝ ሚና ያላቸዉ መሆኑን ገለጹ፡፡ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ዛሬ ግንቦት 8/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ዓለም አቀፍ የስብሰባ ማዕከል የተጀመረዉን የምስራቅ አፍሪካ ትልቁ የቴክኖሎጂ ኤክሲፖ (ኢቴክስ ኤክስፖ 2025) ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋትና ለሀገሪቱ ልማት ላይ…

የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን እና የኢትዮጵያዊያንን ዉበት የሚያጎላ ነው፡
|

የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን ህብረ-ብሔራዊ አንድነትን እና የኢትዮጵያዊያንን ዉበት የሚያጎላ ነው፡

ኢትዮጵያ የብዝኃ ቋንቋ፣ ብዝኃ ባህልና ብዝኃ ማንነት ሃገር ናት፡፡ ብዝኃነት ለኢትዮጵያዊያን ተፈጥሯችን፣ ዉበታችንና የጥንካሬአችን ምንጭ ነው፡፡ ብዝኃ ማንነት ያለበት ሕዝቦች ሀገር መሆናችን ጸጋችን ነው፤ ብዝኃነት የኢትዮጵያ ተጨባጭ እዉነታና ውብትም ነው፡፡ በኢትዮጵያ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ሂደት አንድ ጠንካራ ሀገር ለመገንባት በርካታ መንገዶች ተሞክሯል፡፡ ነባሩንና ተፈጥሯችን የሆነውን ብዝኃ ማንነትን በአንድ ወጥ ማንነት ለመቀየር ብዙ ተለፍቶበታል፡፡ በፖሊሲና ተቋማዊ አሰራር…

ለመላው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ2017 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ!
|

ለመላው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ2017 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ!

ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመትን በጉጉት ይጠብቃሉ፤ ጋራ ሸንተረሩም የዚህ አዲስ ዓመት ጠባቂ ይመስል ኩልል ባለ ንጹሕ የምንጭ ውኃ ፏፏቴ፣ በልዩ ልዩ ኅብረ ቀለማት አበቦች ይዋባሉ፡፡ አዲስ ዓመታችን ዐዳዲስ ዕቅዶችን መተግበር የምንጀምርበት፣ ተነፋፍቀዉ የከረሙ ተማሪዎችና መምህራን በጉጉት የሚገናኙበት፣ በመኸር የተዘራዉ የሚያሸትበት፣ ዐዲስ ተስፋና ጉጉት የሚፈነጥቅበት ነው፤ ለዚህም ነው በላቀ ጉጉት የሚጠበቀው፡፡የተጠናቀቀዉ 2016 ዓ.ም በፈተናዎች ውስጥ…

የዛሬ ትጋት ለነገ ትሩፈት ነው!
|

የዛሬ ትጋት ለነገ ትሩፈት ነው!

መላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለጳጉሜ 5 የነገ ቀን እና ለአዲሱ ዓመት ዋዜማ በሠላም አደረሳችሁ! ነገ የጊዜ መቍጠሪያ ብቻ አይደለም፤ ነገ ተስፋ፣ ምኞት፣ ስንቅ፣ ለዛሬ መነሣሣትና ትጋት ምክንያት ጭምር ነው፡፡ ነገ ሁላችንም ለማየት የምንጓጓለት፣ የተሻለ ሕይወትና ስኬት እንዲኖረን የምንመኘዉ መሻታችን ነው፡፡ እንደግለሰብ የተሻለ ነገን እንመኛለን፤ እንደቤተሰብ የተሻለና የጋራ ደስታና ተድላ ያለው ነገን እናልማለን፤ እንደሀገር ሰላም፣ ደስታ፣ ብልጽግና…