መንግሥት በሁሉም መስኮች የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል!
ባለፉት ሀምሳ ዓመታት የኢትዮጵያ ሴቶች ከፍፁም መገለል ተነስተዉ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊና በልማት መስኮች የባለቤትነት ዋስትናን አረጋግጠዋል፡፡ ዛሬ ላይ ሴቶች በሀገሪቱ የፖለቲካ ዐዉድና ልማት ዘርፎች ውስጥ ግንባር ቀደም ሚናን እየተጫወቱም ይገኛሉ፡፡ ይህ ለውጥ የሴቶችን መሠረታዊ መብቶች ከማስጠበቅ ባለፈ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ገጽታ ላይ የሚታዩ ውጤቶችን እንዲጎናጸፉ አስችሏቸዋል፡፡ ሴት መሪዎች ፖሊሲዎችን በመቀረጽ፣ የአገልግሎት አሰጣጥን በማሳለጥ፣ ልማትን በማፋጠን፣ እንዲሁም…
