ዜናዎች

image
ሁለንተናዊ ትብብር የኢትዮ-ቻይና አጋርነት የጀርባ አጥንት ነው
የኢትዮ-ቻይና የንግድ ልዉዉጡ ከ13 ቢሊዮን ዶላር በልጧል ። የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ታኅሳስ 30/2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለው የኢኮኖሚ ትብብር ቀጣይነት ባለው መልኩ እያደገ በመምጣቱ በሁሉቱ ሀገራት ያለዉን የንግድና ኢንቨስትመንት ፍሰትን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስፋፋ አድርጓል፡፡ በዚህም የሁለትዮሽ የንግድ ለዉዉጥ ከ13 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የበለጠ ሲሆን፣ ይህም ቻይና ኢትዮጵያን ዋንኛ የንግድ አጋር በማድርግ ግንኙነቷን እያጠናከረች መሆኑን ማሳያ ነው፡፡ ኢትዮጵያም ከቻይና የምታስገባው ምርት በተጠናቀቀዉ ዓመት መጀመሪያ ላይ ጭማሪ ያሳየ ሲሆን በመጋቢት ወር ብቻ 1.57 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ደርሷል፡፡ ይህም ከባለፈዉ ዓመት ጋር ሲነጻጸር 22% ጭማሪ አሳይቷል። የውጭ ቀጥተኛ የኢንቨስትመንት ፍሰትም ጠንካራ ሆኖ የቀጠለ ሲሆን፣ ቻይና በማኑፋክቸሪንግ፣ በመንገድና ሕንጻ ፕሮጀክት ግንባታዎች ላይ በመሰማራት ግንባር ቀደም ሀገር ሆና እየሰራች ነዉ፡፡ የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞን የሚያፋጥኑ የመሠረተ ልማትና የፋይናንስ ተደራሽነት ማስፋፋት በተለይ ከባቡር ሐዲድ ዝርጋታ፣ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች እስከ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ድረስ የተገኙ ስኬቶች የሁለቱን ሀገራት የኢኮኖሚ አጋርነትን አጠናክሯል፡፡ የኢኮኖሚ ትብብር የዚህ አጋርነት የጀርባ አጥንት ሲሆን፣ በየካቲት 2017 በአዲስ አበባ የተካሄደው የኢትዮ-ቻይና የኢኮኖሚ እና የንግድ ልዉዉጥ መድረክ በኢንቨስትመንት፣ በንግድ እና በአቅርቦት ሰንሰለቶች ላይ ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ይበልጥ ኢንዲጠናክር አድርጓል፡፡ ኢትዮጵያ በዚሁ ዓመት ወደ አዲሱ የዓለም የኢኮኖሚ ጥምረት፣ BRICS+ መቀላቀሏ ለዘመናዊነት እና የቻይናን ጨምሮ ለአለም አቀፍ ገበያዎች ተደራሽ የመሆን እድሎችን አስፍቷል፡፡...