የማኅበረሰብ ሚዲያዉ ብሔራዊ ጥቅሞችን ማስገንዘብ እና የወል ትርክትን ማስረጽ ላይ በትኩረት መሥራት እንደሚገባዉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስገነዘበ፡፡
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ወራቶች ብቻ በርካታ ዲፕሎማቶችን በመቀበል የአለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ስትራቴጂካዊ ማዕከልነቷን በተግባር አረጋግጣለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰሞኑን ከቡሩንዲ፣ከላይቤሪያ እና ከፖርቹጋል ከፍተኛ መሪዎች ጋር በአዲስ አበባ ስኬታማ ውይይት አድርገዋል። ከዚህ በተጨማሪም የብራዚል፣ የቱርክ፣ የማሌዥያ፣ ጣሊያን እና የእስራኤል መሪዎችን እንዲሁም የቻይና እና የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ተቀብለው አነጋግረዋል። እንደ ኬንያ፣…
ሚያዝያ 15/8/2018 ዓ.ም የሀገርን የመረጃ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ በተተገበረው የሦስት ዓመት የስታትስቲክስ ልማት ፕሮግራም፣ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የ2.6 ሚሊዮን የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ እንዲሁም ከ23 ዓመታት በኋላ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ ሀገራዊ የግብርና ቆጠራ በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል። ይህ ርምጃ ሀገሪቱ ከውጭ ተቋማት የመረጃ ጥገኝነት ተላቅቃ የራሷን የኢኮኖሚ ትንበያና ፖሊሲ ደህንነቱ በተጠበቀና አስተማማኝ መረጃ ላይ እንድትመሠርት አቅም የፈጠረ…
የአፍሪካ ኅብረት እና የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድኖች የኢትዮጵያን 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ ሂደት አዎንታዊና ሕጋዊ ማዕቀፉን የተከተለ እንደነበር በመግለፅ ፤ መንግሥት ዴሞክራሲን ለማጎልበት የሰራውን ሥራ አበረታተዋል ። በቀጣይም ተፎካካሪ ፓርቲዎች ቅሬታዎቻቸውን በሕጋዊ መንገድ ብቻ እንዲፈቱ፣ የሴቶች ተሳትፎና የውይይት ባህል ይበልጥ እንዲጎለብት፣ እንዲሁም ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ኢትዮጵያውያን የውስጥ ጉዳያቸውን በራሳቸው እንዲወስኑ ዕድል እንዲሰጥ አሳስበዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች…
የሚዲያ እንዱስትሪዉ በሂደት ወደ ድጂታል እንዲሸጋገር በመንግስት ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በራሱ አቅም ያበለጸገውን የሞባይል መተግበሪያ (አፕ) በዛሬው ዕለት በይፋ አስመርቋል። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) የኢቢሲ የሞባይል መተግበሪያ ማስጀመሪያ ዝግጀት ላይ ተግኝተዉ ባስተላለፉት መልዕክት፣ መንግስት የሚዲያ እንዱስትሪዉን ዐጠቃላይ ወደ የዲጂታል ሽግግር…
መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ የታሪክ አውድ ውስጥ አዲስ ትርጉምና ጽኑ ቃል-ኪዳን ተላብሶ ብቅ ያለ፣ ለሀገራችንና ለሕዝቦቿም አዲስ የተስፋ አድማስን የፈነጠቀ ክስተት ነበር። ይህ ዕለት ኢትዮጵያን ተብትቦ ይዞ ከነበረው ውስብስብ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ቅርቃር አውጥቶ ወደ ብሩህ መጻኢ ዕድል ለማሸጋገር የተገባ ታላቅ የትውልድ…
ኢትዮጵያ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 በተሳካ ሁኔታ በማጠናቀቅ ፣ ዜጎችን ማዕከል በማድረግ ፍትሃዊ ተደራሽነት የሚያሰፋውን፣ በዜጎችና በተቋማት መካከል መተማመንን የሚያሰፋውን ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ ጀምራለች ። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication Post Views: 103