ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርድት ያደረጉት አቀባበል
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication
ሚያዝያ 16/2018 ዓ.ም የሀገራችን የቱሪዝም ዘርፍ በ”ሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም” ማዕቀፍ ውስጥ የኢኮኖሚ እድገታችን ዋነኛ ምሰሶ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በ”ገበታ ለትውልድ” መርሃግብር የተከናወኑ የልማት ስራዎች የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ከዘመናዊ ጥበብ ጋር በማቀናጀት ለኢትዮጵያ አዲስ ገጽታና ክብር እየገነቡ ነው። እነዚህ ፕሮጀክቶች ታሪካዊ እሴቶቻችንን ጠብቆ ለትውልድ ከማሻገር ባለፈ፣ ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንትና የሁነት ቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ በማድረግ የማህበረሰቡን…
ኢትዮጵያ ቀደም ሲል ከነበረው ግትር ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ አስተሳሰብ ተላቃ፣ ትኩረቱን በተግባራዊ አፈጻጸም ላይ ያደረገ አዲስ ገቢር ነበብ የፖለቲካ ኢኮኖሚ እይታ የተቃኘ የፖሊሲ ማዕቀፍ መከተል ከጀመረች ሰነባብታለች። ይኅው አዲስ አቅጣጫ፤ ሀገሪቱ ለወቅታዊ የዓለምና የሀገር ውስጥ ነባራዊ ሁኔታዎች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራዊ መፍትሄዎችን እንድትቀይስ አስችሏታል። በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የሪፎርም ጉዞ፣ መንግሥትንና የግሉን ዘርፍ እንደ ወሳኝ…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው በአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ (Assembly of the AU) ተሾሙ። ሹመቱ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዘርፉ ላሳዩት አመራር እና ኢትዮጵያ በአህጉሩ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች የምትገኘውን የላቀ ሚና እውቅና ለመስጠት ነው። በተላከው የሹመት ደብዳቤ…
“ዛሬ ጠዋት ከፕሬዝደንት ኡመር ጌሌህ የተላከ መልዕክት በመያዝ የመጡትን የጂቡቲ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ እና አለምአቀፍ ትብብር ሚኒስትር አብዱልቃድር ሁሴን ኦማርን በጽሕፈት ቤታችን ተቀብያለሁ። በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ስላለው ትብብርም ተወያይተናል።” ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication
ሚያዝያ 15/8/2018 ዓ.ም የሀገርን የመረጃ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ በተተገበረው የሦስት ዓመት የስታትስቲክስ ልማት ፕሮግራም፣ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የ2.6 ሚሊዮን የኢኮኖሚ ድርጅቶች ቆጠራ እንዲሁም ከ23 ዓመታት በኋላ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ ሀገራዊ የግብርና ቆጠራ በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል። ይህ ርምጃ ሀገሪቱ ከውጭ ተቋማት የመረጃ ጥገኝነት ተላቅቃ የራሷን የኢኮኖሚ ትንበያና ፖሊሲ ደህንነቱ በተጠበቀና አስተማማኝ መረጃ ላይ እንድትመሠርት አቅም የፈጠረ…
አዲስ አበባ 54ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብስባ ውሳኔዎች የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 54ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው በሁለት የፋይናንስ ድጋፍና ብድር ስምምነቶች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያው ለአገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚውል ከፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ የሰማንያ ሚሊዮን (80,000,000) ዩሮ ብድር ስምምነት ነው፡፡ ሁለተኛው…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication
ዛሬ ስራ የጀመረው፣ አስፈላጊ የሆኑ የመንግሥት አገልግሎቶችን በቀጥታ ወደ ማህበረሰቡ ለማድረስ የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው። ለአገልግሎት የተደራጀው አውቶቡስ ሙሉ ቁሳቁስ የተሟላለትና ራሱን የቻለ የአገልግሎት ማዕከል ሆኖ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ቀልጣፋና አስተማማኝ አሰራርን ለማረጋገጥ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ስርዓቶችን አቀናጅቶ የያዘ ነው። አውቶቡሱ የአገልግሎት ፍሰቱን የሚያደራጅ የሰልፍ ማስተናገጃ ስርዓት ያለው ሲሆን፣ የተለያዩ የክፍያ አማራጮችንም አካቷል። ለአገልግሎቱ የሚያስፈልገውን ኃይል በከፊል…
“ዛሬ ጠዋት የስራ ዘመኑን ሶስተኛ የ100 ቀናት የመንግሥት ሥራ አፈፃፀም ከዘጠኝ ወራት አጠቃላይ አፈፃፀም ጎን ለጎን መገምገም ጀምረናል።ለእድገት አመቺ ካልነበረው እና በደካማ የተቋማት እና የፖለቲካ ማዕቀፍ ፣ በታጠረ የግል ዘርፍ ተሳትፎ እንዲሁም ውጤታማ ባልነበረ የቁጥጥር ከባቢ ከሚገለጠው የኢኮኖሚ መልክ ወጥተናል። የግሉ ዘርፍ ደካማ ውድድር ውስጥ ነበር፤ በመንግሥት ሥር የነበሩ በርከት ያለ ቁጥር ያላቸው የንግድ ተቋማትም…
