”የኢትዮጵያን ችግሮች ብቻ ሳይሆን አቅሞቿን መመልከት ይገባናል”

20ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በውቢቱ ሆሳዕና ከተማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በበዓሉ ባደረጉት ንግግር “የኢትዮጵያን ችግሮች ብቻ ሳይሆን አቅሞቿን መመልከት ይገባናል” ብለዋል። በሚቀጥለው ዓመትም የጅማ ከተማ 21ኛውን በዓል እንደምታከብርም በፕሮግራሙ ላይ ተገልጿል። Office of the Prime Minister-Ethiopia

ኢትዮጵያዊነት በኅብር ቀለም!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ኢትዮጵያዊነትን የገለጹበት መንገድ የመደመር ፍልስፍና መሠረት ሲሆን ኢትዮጵያዊነትን በአንድ ወገን ወይም በአንድ ቀለም ሳይሆን፣ በሁለንተናዊ የኅብረት ስብስብ መልክ አስቀምጠዋል። “ኢትዮጵያዊነት በኅብር ቀለም የሚሳል፤ በኅብር ባህል ሚኖር፤ በኅብር ቋንቋ የሚነገር፤ በኅብር ደም የተሠራ፤ በኅብር ላብ የሚገነባ፤ በኅብር ጥበብ የሚሻገር” የሚለው ሐሳብ፣ ብዝኃነትን እንደ ስጋት ሳይሆን እንደ ጥሬ ኃይል (Raw Power) ያሳያል። እያንዳንዱ…

“የኔነት” ሳይሆን “የኛነት”

የኢትዮጵያ ባህላዊ ሀብት እንደ ብሔራዊ መደመር። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት ይህ አጭር ግን ጥልቅ መልእክት፣ የኢትዮጵያን ባህላዊ፣ ታሪካዊና ማኅበራዊ እሴቶች ከጎጥ ወሰን በላይ ያለውን ዋጋ ያሳያል። መልእክቱ የኢትዮጵያዊነትን ትርጉም ከነጠላ ማንነት ወደ የጋራ ንብረትነት በማሸጋገር የብልፅግናን ራዕይ ይደግፋል። ብዝኃነት እንደ የጋራ ሀብትና ባለቤትነት፣ ይህ መልእክት እያንዳንዱ ክልላዊ ወይም ብሔረሰባዊ እሴት ለአንድ ብሔረሰብ ብቻ…

የብሔር፣ ብሔረ-ሰቦችና ሕዝቦች ቀን ሕገ መንግሥታዊ ቃል ኪዳናችንን የምናድስበትና የብዝኃነታችንን ዐቅም የምናልቅበት ቀን ነው!

ኢትዮጵያ በብዙ መልኩ የሚገለጽ ብዝኃነት ባለቤት ናት፡፡ የቋንቋ፣ የባህል፣ የብሔር፣ የሃይማኖት፣ የፖለቲካዊ አመለካከት፣ የዕድሜ፣ የፆታ ወ.ዘ.ተ ብዝኃነቶቿ የሚያስጌጧት ድንቅና ቀደምት ሀገር ናት፤ ኢትዮጵያ፡፡ ይህንን ብዝኃነቷን እንደ እሴት የምታዳብርበት፣ እሴቱን ወደ መፈጸም ዐቅም የምትለውጥበት ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐት ባለቤትም ናት፡፡ ለዚህም ነው የጋራ የቃል ኪዳን ሰነድ በሆነው ሕገ መንግሥታችን አንድ የጋራ የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመገንባት በነፃ…

“ኢትዮጵያ ታላቁ ሕዳሴ ግድብን በራስ ዐቅም ገንብታ ማጠናቀቋ ለአፍሪካ ሌላ ዐዲስ ምዕራፍ ነው፡፡” የፓን አፍሪካኒዝም አቀንቃኞችና የቀድሞ የፍሪካ መሪዎች ቤተሰቦች

ከተለያዩ የአፍሪካ አገራት የተውጣጡ የቀድሞ ፓን-አፍሪካኒዝም አቀንቃኝ መሪዎች ቤተሰቦች እና ጋዜጠኞች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝቱ ወቅት በሰጡት አስተያየትም “ኢትዮጵያ ፓን አፍሪካኒዝምን በላቀ መሠረት ላይ ገንብታዋለች፤ ይህ ለአፍሪካ ሌላ ዐዲስ ምዕራፍ ነው” ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያውያን በራስ ዐቅም እና ጥረት የተገነባዉ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከዓድዋ ድል እና ከአፍሪካ ኅብረት ምሥረታ ቀጥሎ ሦስተኛዉ የፓን አፍሪካኒዝም መሠረት…