“በጂኦ ፖለቲካ ውጥረት እና በኢ-ተገማች ዲፕሎማሲ በሚስተዋልበት ሁኔታ በሀገራችን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብ ችለናል” አቶ አደም ፋራህ

በጂኦ ፖለቲካዊ ውጥረት፣ በኢ-ተገማች የታሪፍ ዲፕሎማሲ፣ በአቅርቦት ሠንሰለት መቆራረጥ ምክንያት በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢኮኖሚ ዕድገት መቀዛቀዝ፣ የተዳከመ የማክሮ ኢክኖሚ ዓውድ በሚስተዋልበት ሁኔታ፣ በሀገራችን ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስቀጠል መቻሉን በምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል ኃላፊ ክቡር አቶ አደም ፍራህ ገለጹ። ለዚህ አመርቂ ውጤት መመዝገብ ያበቃን የሦስት ዋና ጉዳዮች ድምር ውጤት ነው ያሉት አቶ…

“የኮይሻ ፕሮጀክት እንደ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ብቻ ሳይሆን የቱሪዝም መስህብ የሚሆኑ ስራዎች አሉት” ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ

የኮይሻ ፕሮጀክት ከኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫነት ባሻገር የቱሪዝም መስህብ የሚሆኑ ገፅታዎች እንዳሉት የኢፌዲሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ‘የሚኒስትሮች ምክር ቤት ምልከታ በኮይሻ’ በሚል በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መንግስት በለውጡ የታደገው ሌላው ፕሮጀክት የኮይሻን ፕሮጀክት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የዱር እንስሳት መገኛ የሆነው እና አረንጓዴ የለበሰውን የጨበራ ጩርጩራ ለምለም…

ባለፉት 100 ቀናት የዉጭ ቱሪስት ፍሰት በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል- የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)

ባለፉት 100 ቀናት ዉስጥ የዉጭ ቱርዝም ፍሰት ከዕቅድ ከተያዘዉ በላይ በመጨመር በሀገሪቱ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ዉስጥ ከፍተኛ ድርሻ ማበርከቱን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡ በዚህም በ100 ቀናት ብቻ 376ሺህ 615 የዉጭ ቱርስቶች ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል ብለዋል፡፡ ይህም በዕቅድ ከተያዘዉ 150% ማሳካት የተቻለ ሲሆን፣ ከአምና በተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ብልጫ ማሳየቱን ተናግረዋል፡፡ በተለይም ባለፉት…

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የመቶ ቀን እቅድ ግምገማ የአለምን የኢኮኖሚ አዝማሚያ፣ የኢትዮጵያን ማክሮኢኮኖሚ የመጀመሪያ ሩብ አመት አፈፃፀም እንዲሁም የእድገት አዝማሚያን እና አጠቃላይ ምልከታን ያካተተ አቅርቦትን አካትቷል። በአለም የኢኮኖሚ ልማት አውድ ስንመለከት ኢትዮጵያ ልዩ ጥንካሬ እና የእድገት ፍጥነት አሳይታለች። በ2017 የበጀት አመት የኢትዮጵያ አጠቃላይ የኢኮኖሚ አፈፃፀም በጥንካሬው በመቀጠል 9.2 በመቶ አመታዊ የGDP እድገት አሳይቷል። ይኽም 7.3 በመቶ በሆነ ጠንካራ የግብርና ውጤት መስፋፋት፣ በ13 በመቶ የኢንደስትሪ እድገት ብሎም በ7.5 በመቶ የአገልግሎት ዘርፍ እድገት የተገለፀ ነበር። የሀገራችን የGDP ተዋፅኦም በብዝኃ መሠረት እየያዘ መሄዱን የሚያሳይ ሲሆን ይኽም በግብርና 31.3 በመቶ፣ በኢንደስትሪ 30.2 በመቶ እና በአገልግሎት 39.6 በመቶ አስተዋፅኦ የታየ ነው። እየተካሄዱ በሚገኙ የለውጥ ሥራዎች፣ በመንግሥት እየተከወኑ ባሉ የተለያዩ የልማት ሥራዎች እና አዲስ ኢንቨስትመንቶች በመደገፍ በ2018 ዓመተ ምኅረት ኢኮኖሚያችን በ10.2 በመቶ እንደሚያድግ ይጠበቃል። እንደ የታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ያሉ ፕሮጀክቶች መጠናቀቅ ብሎም እንደ የማዳበሪያ ማምረቻ እና የተፈጥሮ ጋዝ ልማት ሥራ ጅማሮዎች የኢኮኖሚ እድገቱን የበለጠ እንደሚያነቃቁ ይጠበቃል። የየዘርፉ የእድገት ትንበያም ጠንካራ ውጤት እንደሚገኝ ያመለክታል። ግብርና በ7.8 በመቶ፣ በአዳዲስ የማኑፋክቸሪንግ ፕሮጀክቶች እና የተሻሻሉ ግብዓቶች የተጠናከረው ኢንደስትሪ 13.2 በመቶ እንደሚያድጉ የተተነበየ ሲሆን ማዕድን ለ2018 የተቀመጠለትን ግብ እንደሚበልጥ ይጠበቃል። በተጨማሪም የአገልግሎት ዘርፉ እድገት በሚያሳዩት የንግድ እንቅስቃሴ፣ የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የቱሪዝም ፍሰት እና የዲጂታል ኢኮኖሚ መስፋፋት በመጠቀም 9.3 በመቶ እንደሚያድግ ይጠበቃል። የውጭ ንግድ 2.5 ቢሊዮን ዶላር የደረሰ ሲሆን ይኽም እቅዱን እና የባለፈውን አመት ተመሳሳይ ጊዜ አፈፃፀም የበለጠ ሆኖ ታይቷል። የፋይናንስ ዘርፉ የልማት ሥራዎችን እና ኢንቨስትመንትን በመደገፍ እና ቁልፍ ሚናውን እየተወጣ ሲሆን በመጀመሪያው ሩብ አመት 113 በመቶ የሆነ ከቀደመው ተመሳሳይ ጊዜ ብልጫ ያለው የብድር አቅርቦት አቅርቧል። የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎትም እየተጠናከረ መሄዱን የቀጠለ ሲሆን በሶስት ወራት ብቻ 6.5 ትሪሊዮን ብር የተንቀሳቀሰበት ደረጃ ደርሷል። አጠቃላይ አፈፃፀሙ በሁሉም መስኮች የተሻለ ውጤትን የሚያሳይ ሲሆን ይኽም ኢትዮጵያ ወደ ኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ብሎም ዘላቂ እና አካታች የኢኮኖሚ እድገት የምታደርገውን ፈጣን ሂደት የሚያረጋግጥ ነው። The Council of Ministers’ 100 Days Review included a presentation on global economic trends, Ethiopia’s macroeconomic performance over the past quarter, and growth trend and outlook. In the context of global economic developments, Ethiopia continues to demonstrate distinctive resilience and momentum. Ethiopia’s overall economic performance has remained strong, recording a 9.2% annual GDP growth in the 2017 Ethiopian fiscal year, driven by robust expansion in agriculture (7.3%), industry (13%), and services (7.5%). The nation’s GDP composition reflects this diversification, with agriculture contributing 31.3%, industry 30.2%, and services 39.6%. Looking ahead, the economy is projected to grow by 10.2% in E.C 2018, supported by ongoing reforms, government-led initiatives, and new investments. Major projects such as the completion of the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD), alongside new mega investments in fertilizer production and gas development, are expected to further stimulate economic growth. Sectoral forecasts remain robust and strong: agriculture is projected to expand by 7.8%, industry by 13.2%, driven by new manufacturing projects and improved input supply, while mining is expected to exceed 2018 performance targets. Additionally, the services sector is forecasted to grow by 9.3%, fueled by increasing trade activity, transport, tourism inflows, and digital economy expansion. Commodity exports stood at 2.5 billion USD, surpassing target as well as last year’s similar quarter performance. The finance sector is playing its key role in financing development and investment as demonstrated by a 113% higher loan disbursement in the past quarter as compared to similar time last year. The digital finance continues to gain traction, with transactions valued at 6.5 trillion birr in just three months. The overall performance indicates a better outlook on all fronts underscoring Ethiopia’s accelerating momentum toward structural transformation, sustainable and inclusive economic growth. #PMOEthiopia

በኢትዮጵያ በዲጂታል ጤናው ዘርፍ፣ በሰው ሀብት ልማት እና በጤና ፋይናንስ ማሻሻያ ስራዎች ዙሪያ  ተጨባጭ ለዉጦች ተመዝግበዋል ፡፡

የኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር ከክልል ጤና ቢሮዎችና የልማት አጋሮች ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 27ኛው ዓመታዊ የጤና ሴክተር የምክክር ጉባኤ ካዘሬ ጥቅምት 12/2018 ዓ.ም በጅማ ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡ ጉባኤዉ በሀገር አቀፍ የጤና ግቦችና እና የማሻሻያ ክንዉኖችን፣ እንዲሁም ቀጣይ የዘርፉ አቅጣጫዎችን ለመገምገም ዓላማ ያደረገ ሲሆን፣ በተለይም በመንግስትና ባለድርሻ አካላት መካከል ያለውን ቅንጅታዊ አሰራርን ከማጎልበት ባሻገር በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ  ፈጠራን…

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 49ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ።

ምክር ቤቱ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች፡- 1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የኢትዮጵያ ኒውክሊየር ኃይል ኮሚሽን ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ነው፡፡ ኮሚሽኑ ሀገራችን የኒውክለር ቴክኖሎጂን ለሰላማዊ መንገድ ከዓለም አቀፍ ማዕቀፎች ጋር በተጣጣመ መልኩ በኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት፣ በኢንዱስትሪ ልማት፣ በምግብ ዋስትና፣ በጤና አገልግሎት፣ በሳይንስ እና ምርምር ዘርፎች ላይ ለመጠቀም የምታደርገውን ጥረት የመምራትና…

National Initiatives Strengthening Ethiopia’s Economy and Honoring Its Flag

The 18th National Flag Day has celebrated with great passion at the Government Communication Service today. Honorable Minister Enatalem Melese emphasized that milestones such as the Adwa Victory, the construction of the Grand Renaissance Dam, and the initiation of gas extraction and fertilizer production are pivotal in restoring Ethiopia’s economic strength and uplifting the dignity…

የሰንደቅ አለማ ልዕልና የሚገለጠው ሰንደቅ አለማውን በሰቀልንበት የከፍታ ማማ ነው ።

ሠንደቅ ዓላማ የብሔራዊ አንድነት መገለጫ፤ የአንድ አገር ዜጎች አገራዊ ፍቅርና ብሔራዊ ስሜትን የሚገልፁበት፤ ታሪካዊ ትስስርና  ስነ-ልቦናዊ አንድነት  የሚንፀባረቁበት የአገራዊ አንድነትና ህብረት አርማ ነው። በአገራችን ኢትዮጵያ ለአስራ ስምንተኛ /18ኛ/ ጊዜ “ሰንደቅ ዓለማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ  የክፍታ ዘመን ብስራት ለብሔራዊ አንድነታችን ፣ለሉዐላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ !” በሚል መሪ ቃል እየተከበረ የሚገኘውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ጥቅምት…

|

ስኬቶቻችን የሰንደቃችን ከፍታ የሚጨምሩ ናቸው

********************************** ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት እመርታዊ ስኬቶችን እያስመዘገበች የሚመጥናትን ከፍታ እየያዘች ትገኛለች። ለዘመናት የቁጭት እና እንጉርጉሮ ትርክት ምንጭ የነበረዉን ዓባይን ገርታ የኃይል እና ብርሃን ምንጭ አድርጋለች፡፡ በንጋት ኃይቅ በምግብ ሉዓላዊነቷ ላይ ጉልህ ሚና የሚጫወት የዓሣ ምርት ማግኘት ችላለች፤ ዐዲስ የቱሪዝም መዳረሻ ደሴቶችንና ከተሞችን ፈጥራለች፡፡ የዓባይን የቁጭት ትርክት ወደ ድል እና አሸናፊነት ብስራት ቀይራለች፡፡ ተጨማሪ…

ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ረቡዕ እለት በሀላባ እና ከምባታ ዞኖች የሞዴል የገጠር መንደሮችን ማስረከባቸው የሚታወስ ሲሆን ዛሬ ደግሞ በሀዲያ እና ስልጤ ዞኖች የተገነቡትን አስረክበዋል።

ረቡዕ በሀላባ እና ከምባታ ዞኖች የነበረንን የሞዴል የገጠር መንደሮች ርክክብ ሥነሥርዓት በመቀጠል ዛሬ ደግሞ በሀዲያ እና ስልጤ ዞኖች የተገነቡትን አስረክበናል። እነኚህ ባለሶስት መኝታ ቤት መኖሪያዎች ለማብሰል የሚያገለግል የባዮጋዝ መሣሪያ፣ የፀኃይ ኃይል ማመንጫ፣ የዶሮ ማርቢያ፣ የተለየ የእንስሳት በረት የተሟላላቸው ሲሆን በተመጣጣኝ አነስተኛ ወጪ ከአካባቢ በሚገኙ ግብዓቶች የተሻለ መኖሪያ ከማስገኘት አንፃር ለገጠሩ ማኅበረሰብ ብልጽግና ያለንን ሕልም የሚያሳይ…