የኑሮ ውድነትንና የዋጋ ንረትን ለመቀነስ መንግሥት ምን አደረገ ?

“የኑሮ ውድነት የበርካታ ሀገራት ፈተና ሆኖ ቀጥሏል፡፡ በአንዳንድ ሀገራት ከ400 ፐርሰንት በላይ የደረሰ የዋጋ ንረት እየተመዘገበ ነው፡፡ ከአፍሪካም 172 ፐርሰንት የደረሰ የዋጋ ንረት ያጋጠመ ሲሆን በጎረቤት ሀገራት እንኳን 72 ፐርሰንት የደረሰ የዋጋ ግሽበት ተመዝግቧል ። ከለውጡ ወዲህ መንግሥት አለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን ቀድሞ በመገምገም ዜጎች ላይ የሚደርሰውን የኑሮ ውድነት ጫናን በዘላቂነት ለመቀነስ በርካታ ኢንሼቲቮችን ቀርጾ…

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የመቶ ቀን እቅድ ግምገማ የአለምን የኢኮኖሚ አዝማሚያ፣ የኢትዮጵያን ማክሮኢኮኖሚ የመጀመሪያ ሩብ አመት አፈፃፀም እንዲሁም የእድገት አዝማሚያን እና አጠቃላይ ምልከታን ያካተተ አቅርቦትን አካትቷል። በአለም የኢኮኖሚ ልማት አውድ ስንመለከት ኢትዮጵያ ልዩ ጥንካሬ እና የእድገት ፍጥነት አሳይታለች። በ2017 የበጀት አመት የኢትዮጵያ አጠቃላይ የኢኮኖሚ አፈፃፀም በጥንካሬው በመቀጠል 9.2 በመቶ አመታዊ የGDP እድገት አሳይቷል። ይኽም 7.3 በመቶ በሆነ ጠንካራ የግብርና ውጤት መስፋፋት፣ በ13 በመቶ የኢንደስትሪ እድገት ብሎም በ7.5 በመቶ የአገልግሎት ዘርፍ እድገት የተገለፀ ነበር። የሀገራችን የGDP ተዋፅኦም በብዝኃ መሠረት እየያዘ መሄዱን የሚያሳይ ሲሆን ይኽም በግብርና 31.3 በመቶ፣ በኢንደስትሪ 30.2 በመቶ እና በአገልግሎት 39.6 በመቶ አስተዋፅኦ የታየ ነው። እየተካሄዱ በሚገኙ የለውጥ ሥራዎች፣ በመንግሥት እየተከወኑ ባሉ የተለያዩ የልማት ሥራዎች እና አዲስ ኢንቨስትመንቶች በመደገፍ በ2018 ዓመተ ምኅረት ኢኮኖሚያችን በ10.2 በመቶ እንደሚያድግ ይጠበቃል። እንደ የታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ያሉ ፕሮጀክቶች መጠናቀቅ ብሎም እንደ የማዳበሪያ ማምረቻ እና የተፈጥሮ ጋዝ ልማት ሥራ ጅማሮዎች የኢኮኖሚ እድገቱን የበለጠ እንደሚያነቃቁ ይጠበቃል። የየዘርፉ የእድገት ትንበያም ጠንካራ ውጤት እንደሚገኝ ያመለክታል። ግብርና በ7.8 በመቶ፣ በአዳዲስ የማኑፋክቸሪንግ ፕሮጀክቶች እና የተሻሻሉ ግብዓቶች የተጠናከረው ኢንደስትሪ 13.2 በመቶ እንደሚያድጉ የተተነበየ ሲሆን ማዕድን ለ2018 የተቀመጠለትን ግብ እንደሚበልጥ ይጠበቃል። በተጨማሪም የአገልግሎት ዘርፉ እድገት በሚያሳዩት የንግድ እንቅስቃሴ፣ የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የቱሪዝም ፍሰት እና የዲጂታል ኢኮኖሚ መስፋፋት በመጠቀም 9.3 በመቶ እንደሚያድግ ይጠበቃል። የውጭ ንግድ 2.5 ቢሊዮን ዶላር የደረሰ ሲሆን ይኽም እቅዱን እና የባለፈውን አመት ተመሳሳይ ጊዜ አፈፃፀም የበለጠ ሆኖ ታይቷል። የፋይናንስ ዘርፉ የልማት ሥራዎችን እና ኢንቨስትመንትን በመደገፍ እና ቁልፍ ሚናውን እየተወጣ ሲሆን በመጀመሪያው ሩብ አመት 113 በመቶ የሆነ ከቀደመው ተመሳሳይ ጊዜ ብልጫ ያለው የብድር አቅርቦት አቅርቧል። የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎትም እየተጠናከረ መሄዱን የቀጠለ ሲሆን በሶስት ወራት ብቻ 6.5 ትሪሊዮን ብር የተንቀሳቀሰበት ደረጃ ደርሷል። አጠቃላይ አፈፃፀሙ በሁሉም መስኮች የተሻለ ውጤትን የሚያሳይ ሲሆን ይኽም ኢትዮጵያ ወደ ኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ብሎም ዘላቂ እና አካታች የኢኮኖሚ እድገት የምታደርገውን ፈጣን ሂደት የሚያረጋግጥ ነው። The Council of Ministers’ 100 Days Review included a presentation on global economic trends, Ethiopia’s macroeconomic performance over the past quarter, and growth trend and outlook. In the context of global economic developments, Ethiopia continues to demonstrate distinctive resilience and momentum. Ethiopia’s overall economic performance has remained strong, recording a 9.2% annual GDP growth in the 2017 Ethiopian fiscal year, driven by robust expansion in agriculture (7.3%), industry (13%), and services (7.5%). The nation’s GDP composition reflects this diversification, with agriculture contributing 31.3%, industry 30.2%, and services 39.6%. Looking ahead, the economy is projected to grow by 10.2% in E.C 2018, supported by ongoing reforms, government-led initiatives, and new investments. Major projects such as the completion of the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD), alongside new mega investments in fertilizer production and gas development, are expected to further stimulate economic growth. Sectoral forecasts remain robust and strong: agriculture is projected to expand by 7.8%, industry by 13.2%, driven by new manufacturing projects and improved input supply, while mining is expected to exceed 2018 performance targets. Additionally, the services sector is forecasted to grow by 9.3%, fueled by increasing trade activity, transport, tourism inflows, and digital economy expansion. Commodity exports stood at 2.5 billion USD, surpassing target as well as last year’s similar quarter performance. The finance sector is playing its key role in financing development and investment as demonstrated by a 113% higher loan disbursement in the past quarter as compared to similar time last year. The digital finance continues to gain traction, with transactions valued at 6.5 trillion birr in just three months. The overall performance indicates a better outlook on all fronts underscoring Ethiopia’s accelerating momentum toward structural transformation, sustainable and inclusive economic growth. #PMOEthiopia

ኢትዮጵያን የምስራቅ አፍሪካ የታዳሽ ሀይል ምንጭ ለማድረግ የተጀመረው ጉዞ አካል የሆነው የኮይሻ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ገጽታ!

ዛሬ የ2018 ዓመተ ምህረት የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ የጀመርነው የኮይሻ የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ፕሮጀክት በመጎብኝት ነው።

ፕሮጀክቱ ባለፈው ከነበረኝ ጉብኝት በኋላ የሚለካ የሥራ እድገትም ታይቶበታል። የግድቡ ከፍታ 128 ሜትር የደረሰ ሲሆን አጠቃላይ የሲቪል ሥራው 70 ከመቶ ደርሷል። ይኽ ስኬት ለኃይል ምንጭ ዋስትናችን ላለን ያላሰለሰ ጽኑ ጥረት ምስክር የሚሆን ነው። Today, we begin the Council of Ministers’ macroeconomic evaluation for the first 100-days of the Ethiopian calendar year 2018 with a visit…

በኃብት ስጦታ አንፃር ስንመለከት ኢትዮጵያ ለሁሉም የሚበቃ ኃብት እንዳላት እናውቃለን። በባሌ ዞን ከተለያዩ አመራሮች ጋር ያደረግነው ጉብኝት የመጨረሻ መዳረሻ አስደማሚው የፊንጫ ሀበራ ፏፏቴ ሆኗል። በግርማ የሚወርደው ፏፏቴ ወደ ሶፍኡመር የዋሻ ሥርዓት የሚደመረውን የወይብ ወንዝ የሚቀላቀል ነው። የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮ የሚገኝበት ይኽ አስደናቂ ከባቢ ድንቅ የአዕዋፍ መገኛና በቅርቡ የዋሻ መስህብ የተገኘበት እንዲሁም የራፉ ውብ የዐለት ደን አቅራብያ የሚገኝ ነው። በቅርቡ በአካባቢው የሚገነባው ማረፊያ ሲጠናቀቅም ለጎብኝዎች የበለጠ ሳቢ እና ምቹ ይሆናል።

ባለፉት ሶስት ቀናት በጉብኝቱ የተሳተፉ የቀድሞ እና በሥራ ላይ ያሉ ኃላፊዎች በጉብኝቱ የተመለከቱት የተፈጥሮ፣ የባሕል እና የሰው ኃብት ከፍ ያለ መነሳሳትን ፈጥሮላቸዋል። የጋራ ሥራችን እነዚህን ኃብቶቻችንን መግለጥ፣ ማሳደግ፣ በኃብቶቹ ላይ በመጨመር ቀጣዩ ትውልድ ችቦውን ተረክቦ እንዲቀጥል መሠረት መጣል ነው። ኢትዮጵያ በርግጥም የተትረፈረፈ ኃብት ምድር ናት። እንሰባሰብ። ለማለም እንድፈር። የጋራ ነጋችንን በጋራ እንገንባ። Gama qabeenyaatiin yoo…

በባሌ ዞን በነበረን የሁለተኛ ቀን ቆይታ የወልመል ወንዝ የመስኖ ልማት እና ተጠቃሚ አርሶ አደሮች ጉብኝት ባሻገር ወደ ባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሀረና ክላስተር በመገኘት ምልከታ አድርገናል። እነዚህ በግንባታ ላይ በባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ያሉ ፕሮጀክቶች በሃረና ደን የሪራ ኢኮ ሎጅ እና ከባቢውን ብሎም የመመገብያ ስፍራዎችን፣ በእግር እና መኪና መንገዶች የቡና ሱቆችን፣ የምግብ አዳራሾችን እስከ ቱሉ ዲምቱ የከፍታ መወጣጫ ስፍራዎች የሚያካትቱ ናቸው። እነዚህ የልማት ሥራዎች ዘላቂ የቱሪዝም ፕሮጀክቶች የአካባቢ የሥራ ፈጠራ ዕድልን የሚያሰፉ እና የጎብኝዎችን ዕድል የሚያሰፉ በመሆኑ በልዩ ምልከታ የሚታዩ ናቸው።

Turtii keenya guyyaa lammaffaa Godina Baaleetti gooneen Misooma Jallisii Laga Walmal eebbifnee qonnaan bultoota achirraa fayyadaman edda daawwannee booda, piroojektii misooma tuuriizimii haaraa kilaasterii Harannaa gamaaggamuuf gara Paarkii Biyyaalessaa Gaarreewwan Baaleetti deebine. Piroojektiin wayita ammaa hojjetamaa jiru kun Loojii Ikkoo Harannaafi naannawaasaa akkasumas bakkeewwan tajaajila nyaataa, daandiiwwan lafoofi konkolaataa, suuqiiwwan bunaa, bakkeewwan kora Tulluu Diimtuu…

ዛሬ ማለዳ በባሌ ዞን፣ ደሎ መና ወረዳ በመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አማካኝነት የተጀመረውን የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክትን መርቀናል። ፕሮጀክቱ የወልመል ወንዝን በመስኖ በሚገባ በመጠቀም የግብርና ምርታማነትን በማላቅ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተከናወነ ነው። ፕሮጀክቱ ዘላቂ የገጸምድር የመስኖ ሥርዓት በመገንባት የግብርና ስራው ለዘመናት በዝናብ ውሃ ላይ ተመስርቶ የነበረውን የአካባቢውን ሕዝብ ዘላቂ የኑሮ ዘዴ ለማጎናፀፍ ታልሞ ተከናውኗል።

ፕሮጀክቱ በሙሉ አቅሙ ወደ ተግባር በሚገባበት ወቅት 20,000 ለሚሆኑ አርሶአደሮች ለሚያገለግል 9687.45 ሄክታር የእርሻ መሬት አስተማማኝ የመስኖ አቅርቦት ይኖረዋል። ይኽም የግብርና ምርታማነትን የሚያሳደግ፣ ለድርቅ የማይበገር ከባቢን የሚፈጥር ብሎም በማኅበረሰቡ አዳዲስ የሥራ እድል የሚፈጥር ይሆናል። ከነዚህ ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ባሻገር የአካባቢውን የውሃ አስተዳደር ተቋማትን በማጠናከር፣ የአካባቢውን ሕዝብ ባለቤትነት በማሳደግ ብሎም የወልወልን ወንዝ ዘላቂ አጠቃቀም በማጎልበት የተሻለ የምግብ…