የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ለክቡር አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ላበረከቱት አስተዋጽኦ የምስጋና እና የሽኝት መረሃ ግብር አደረገ

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ለክቡር አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በእስካሁኑ ለተቋሙ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የምስጋና እና የሽኝት መረሃ ግብር አድርጓል፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ከበደ ዴሲሳ በመረሃግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ክቡር አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ተቋሙ ከተመሰረተ ጊዜ ጀምሮ ለሀገሪቱ ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ትልቅ አሻራ ማስቀመጣቸዉን ገልጸዋል፡፡ አገልግሎቱ በ2014 ዓ.ም እንደ አዲስ ሲመሰረት ከምንም በመነሳት…

ጠቅላይሚኒስትር ዐቢይ  አሕመድአራተኛውን “የመደመር መንግስት”  የተሰኘዉን መጽሐፍ አስመረቁ

መስከረም 6/2017 ዓ.ም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ  አሕመድ አራተኛውን “የመደመር መንግስት”  የተሰኘዉን መጽሐፍ በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬክሽን ማዕከል በትላንትናው ዕለት በይፋ አስመርቀዋል፡፡ አድሱ መጽሐፍ በኢትዮጵያ ብልጽግና ጉዞ ዉስጥ የተገኙ ሁሉ አቀፍ ዉጤቶችና ተግዳሮቶች፣ እድሎችና ስጋቶች፣ እንዲሁም ተጨባጭ መፍትሔዎችን በማቅረብ የመደመር ፍልስፍናን በጥልቀት የሚተነትን ነዉ፡፡ በተለይም መጽሐፉ በዲጂታል ኢትዮጵያ የታገዘ ቀልጣፋ የህዝብ አስተዳደር ገጽታ፣ ሀገራዊ አንድነት እና…

ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ ነገዋን እየሠራች ነው!

ኢትዮጵያ ነገዋን ዛሬ ላይ ለመሥራት እያደረገች ያለውን ጥረት እና የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማስተዋወቅ 5ኛዉን የጳጉሜን ቀን “የነገዉ ቀን” በሚል ስያሜ እና “ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ” በሚል መሪ መልእክት እያከበረች ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከራሷ ባሻገር የአፍሪካን ማንሰራራት ለማብሰር ዛሬ ላይ ነገዋን እየሠራች ነው፡፡ ለአምስተኛዉ የኢንዱስትሪ አቢዮት የሚመጥን ትውልድ መቅረጽን፣ ለኢንዱስትሪ ዕድገቱ የሚመጥን ታዳሻ ኃይል ማቅረብን፣ የዘመኑ ከተሞችን መፍጠርን፣…

ኢትዮጵያ የምታስተናግደዉ 2ኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባዔ ሀገራችን ያሳካቻቸው ተጨባጭ ልምዶችን የምታካፍልበት መድረክ ነው፡:

********************************* 2ኛዉ የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ይህንን ጉባኤ የምታስተናግደዉ ለተሳታፊዎች ተጨባጭ ልምዶችን በማካፈል ጭምር ነው፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት ሰባት ዓመታት ብቻ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እየሠራች ትገኛለች፡፡ መላዉ ኢትዮጵያውያን በተከታታይ ዓመት በሚያደርጉት የላቀ ተሳትፎ የራሳቸዉን ክብረ ወሰን እያሻሻሉ በአንድ ጀምበር ከ700 ሚሊዮን በላይ…

እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!

 ******************* እንኳን ጳጉሜን 3 የእመርታ ቀን አደረሳችሁ! የእመርታ ቀንን የምናከብረዉ የጀመርነዉን የከፍታ ጉዞ በማላቅ እና በማጽናት የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በተጠናቀቀዉ በጀት ዓመት በበርካታ እመርታዊ ለውጦችን አስመዝግባለች፡፡ ወደተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ውስጥ ገብታ ያለመችዉን አሳክታለች፡፡ የተረጋጋ ማክሮ–ኢኮኖሚ መፍጠር፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ፣ የኢንዱስትሪ ምርቶችን ተወዳዳሪነትና የገበያ ድርሻ ማሳደግ፣ የማዕድን ዘርፉን ዐቅም እና ሕጋዊ ሥርዐት…

ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ያላት ብዝኃነት ልዩ ዐቅም የሚፈጥርላት መሆኑ ተገለፀ።

“ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በሚል መሪ መልእክት የኅብር ቀን በመላዉ ኢትዮጵያ እየተከበረ ነው፡፡ ብዝኃነትንና ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን በጠንካራ መሠረት ላይ ለመገንባት የሚያስችል፣ ብዝኃነት ለኢትዮጵያ ያበረከተዉን ፋይዳ እና በቀጣይም በላቀ ደረጃ እንዴት መጠቀም እንደሚገባ የሚያስገነዘብ የፓናል ውይይት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ መኮንን አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ የፓናል ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የሰላም ሚኒስትር ክቡር አቶ መሐመድ እድሪስ ጥንታዊና ገናና ታሪክ…

“ብዝኃነት ዐቅም፣ ውበት እና ጌጥ ነው፡፡” የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

“ብዝኃነት ዐቅም፣ ውበት እና ጌጥ ነው፤ በዚያዉ ልክ ልንጠቀምበት ይገባል” ሲሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ድኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ አስገነዘቡ፡፡ “ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በሚል መሪ መልእክት የኅብር ቀን በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ተከብሯል፡፡ በመድረኩ ላይ መልእክት ያስተላለፉት ክቡር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ብዝኃነት የተሰናሰነ ዐቅም መኾኑን በመረዳት የማንነት፣ የሐሳብ፣ የታሪክ፣ የባህል እና የመሳሰሉትን ብዝኃነቶች የሚያስተናግድ ሥርዐት እየዳበረ እንደሚገኝ…

ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ እና ዐቅም ነው! ********************************

ኢትዮጵያ በሕዝቦቿ ብዝኃ ማንነት ደምቃ፣ ፀንታና ታፍራ የኖረች፣ ብዝኃ የተፈጥሮ ሀብት ባለቤት የሆነች ድንቅ ሀገር ናት፡፡ ብዝኃነታችን የጥንካሬያችን፣ የሥልጣኔያችን፣ የአይበገሬነታችን፣ የክብራችን፣ የነፃነታችን እና የአልሸነፍ ባይነታችን ምሥጢር ነው፡፡ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የሚገኙ ጥንታዊ ሃይማኖታዊ እና ታሪካዊ ቦታዎች እና የኪነ ሕንጻ ሀብቶቻችን የብዝኃነታችን ውጤቶች ናቸው፡፡ የአክሱም ሐውልቶች፣ የጢያ ትክል ድንጋዮች፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የለጋ ኦዳ ዋሻ…

ፈታናዎችን በመገንዘብና የመሻገሪያ መንገዶችን ለመተለም ዜጎች ምንጊዜም ንቁ መሆን አለባቸዉ- ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር)

በመጪዉ ዓመት የሚኖሩ ፈታናዎችን አስቀድሞ በመገንዘብና የመሻገሪያ መንገዶችን ለመተለም ዜጎች ምንጊዜም ንቁ መሆን አለባቸዉ ሲሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ የዘንድሮ የጷጉሜን ቀናት ስያሜን ተንተርሶ በሀገራዊ ጉዳዮች  ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በዚህም የተጠናቀቀዉ በጀት ዓመት ሀገሪቱ ዉስብስብ ችግሮችን በመሻገር በሁሉም ዘርፎች አኩሪና እምርታዊ ድሎች ያስመዘገበችበት ዓመት እንደ ነበር አስታዉሰዋል፡፡…

የተዋሐደች እና የበለጸገች አፍሪካን እውን ለማድረግ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት በአፍሪካ ሕዝቦች መካከል ድልድይ መገንባትና ትስስር ማጠናከር ላይ መሥራት አለባቸው፡- ዶ.ር ለገሠ ቱሉ

ቀን-21-12-2017 የአፍሪካ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተቋማት የኅብረቱ አጀንዳ 2063 እንዲሳካ የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ እና ባህል ትስስር መጠናከር ላይ እንዲያተኩር የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ.ር) አሳሰቡ፡፡ 15ኛዉ የምሥራቅ አፍሪካ የኮሙኒኬሽን ማኅበር (East African Communication Association) ኮንፈረንስ አዲስ አበባ ላይ እየተካሄደ ነው፡፡ በኮንፈረንሱ መክፈቻ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሠ ቱሉ (ዶ.ር)…