ሁለተኛው ምዕራፍ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ በተግባር!

‎‎ለዘመናት የቆየውን የኢኮኖሚ መዛባቶችን እና የመንግሥት ጥብቅ ቁጥጥር ለመቀልበስ በ2011 ዓ.ም. የተጀመረው የመጀመሪያው ምዕራፍ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ በስንዴ ምርትና በቴሌኮም ዘርፍ ታሪካዊ ስኬቶችን አስመዝግቧል። በእነዚህ ስኬቶች ላይ በመመሥረት የተጀመረው ሁለተኛው ምዕራፍ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ በማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት፣ በንግድ ሥነ ምህዳር፣ እና በዘርፎች ተወዳዳሪነት ላይ በትኩረት እየሠራ ይገኛል። የዚህ ማሻሻያ ቁልፍ ማረጋገጫ…

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

“የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ለአየር ንብረት ጥበቃ ከሚያበረክተው መሠረታዊ አስተዋፅዖ ባለፈ፣ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የማር ምርት ላይ ተጨባጭ ውጤቶችን እያስመዘገበ ይገኛል። ተፈጥሮንና አካባቢያችንን በመጠበቃችን፣ ደኖች እየተስፋፉ በመምጣታቸው፣ የንብ ዝርያዎችን የሚያግዙና የማር ምርትን የሚያሳድጉ ምቹ ከባቢዎች ምክንያት የምግብ ምንጮች ሊፈጠሩ ችለዋል። ‎ተስፋን እንትከል!”

የኢትዮጵያ ዓለም አቀፋዊ ተሰሚነት እያደገ መጥቷል

’ኢትዮጵያ ታከናውናለች’ ብሔራዊ ጉባኤ ላይ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በምክትል ዋና ጸሐፊ ማዕረግ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት የተከበሩ ክላቨር ጋቴቴ ንግግር አድርገዋል። ‎ዋና ስራ አስፈጻሚው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃግብርን፣ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ የተመሰረተውን የኃይል ሽግግር፣ በኢ-ሞቢሊቲ የሚመራውን የትራንስፖርት ዘርፍ ለውጥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድን ቀጣይነት ያለው እድገት በመጥቀስ ኢትዮጵያን በአዎንታዊ የለውጥ ተሞክሮነት…

“ኢትዮጵያ ታከናውናለች” ብሔራዊ ጉባኤ !

“ኢትዮጵያ ታከናውናለች” ብሔራዊ ጉባኤ !

‎”የጀመርናቸው ለውጦች በራሳቸው የመጨረሻ ግብ አይደሉም፤ ይልቁንም ከእኛ በኋላ ለሚመጡት ተከታታይ ትውልዶች የምንጥለው ጠንካራ መሠረት ነው።” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ‎

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የመሠረተ-ልማት የለውጥ ጉዞ

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ በሰጡት ማብራሪያ፣ የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት ጉዞ ለዘመናት ከዘለቀው ሀገራዊ ትልም ተነሥቶ አሁን ላይ በትጉህና ግልጽ መርሆዎች እንዲሁም በተዋቀረ አፈጻጸም ወደሚመራ የለውጥ ዘመን ተሸጋግሯል፤ ለዚህ ስኬት ደግሞ የለውጡ መንግሥት ሀገራዊ ተስፋን ከተቋማዊ አቅም ጋር ወደሚያጣጥም፣ ይበልጥ አመቺ፣ ቅደም ተከተላዊ እና የፋይናንስ ሥነ-ሥርዓትን ወደ ተከተለ አካሄድ ቁርጠኛ ሽግግር ያደረገ…

የማዕድን ዘርፉ ያላንን የተፈጥሮ ሀብት ወደ ተጨባጭ ብሔራዊ ዕድገት እየቀየረው ነው

በማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት ኢንጂነር ሐና ብርሃኑ፣ በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ከነበረበት ደካማ አፈጻጸም ተነስቶ አሁን ላይ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አንዱ መሆን የቻለበትን የማዕድን ትራንስፎርሜሽን ጉዞ አቅርበዋል። ‎ በቁርጠኛ ማሻሻያዎች፣ በገበያ መልሶ ማዋቀር እና እሴትን መጨመር በሚያስችሉ ኢንቨስትመንቶች በመታገዝ ዘርፉ ከፍተኛ የወጪ ንግድ ገቢን እያስገኘ፣ የገቢ ምርቶችን ጥገኝነት እየቀነሰ እና ለኢንዱስትሪ ልማት አዳዲስ…

የኢትዮጵያ ግብርና፦ ከእጅ ወደ አፍ ልምምድ ወደ ንግድ እና ሉዓላዊነት መሠረት

የግብርና ትራንስፎሜሽን ኢንስትቲዩት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ማንደፍሮ ንጉሴ፣ የግብርና ዘርፍ የለውጥ ጉዞን በተመለከተው ማብራሪያ፤ ኢትዮጵያ ስልታዊ ኢንቨስትመንቶችን እና ጉልህ ማሻሻያዎችን በማከናውን የሀገሪቱን የግብርና ዘርፍ ከነበረበት ከእጅ ወደ አፍ ልምምድ ተላቃ አሁን ላይ ከእርሻ ወደ ንግድ ብሎም የሉዓላዊነት መሰረት የተሸጋገረ መሆኑን አመላክተዋል፤ ‎‎ለዚህም ከ10 ዓመቱ መሪ እቅድ ጋር የተጣጣሙ ስትራቴጂዎችንና የፖሊሲ ለውጦ ማዕቀፎችን በመንደፍ፤ የመንግሥት፣…

ዲጂታል ኢኮኖሚን ወደ ምርታማነት የመቀየር ሂደት በኢትዮጵያ

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዲጂታል አማካሪ የሆኑት ሚሪያም ሰዒድ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ተበታትነው የነበሩ አሠራሮችን በዲጂታል ማንነት፣ በክፍያ እና በዳታ ልውውጥ የተቀናጁ የኢኮኖሚ መዋቅሮች ውስጥ በማስገባት፣ የመንግሥት አገልግሎቶችን በማገናኘት እንዲሁም የሃገር በቀል አቅምን በጋራ በማሳደግ፣ ለሰው ሠራሽ አስተውሎት ምቹ የሆነ የኢኮኖሚ መሠረት እየጣለችና ይሄንኑ ሪፎርም ወደ ምርታማነት እየቀየረች እንደምትገኝ አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ አዲስ የከተማ ልማት ምዕራፍ ውስጥ እየገባች ትገኛለች

በገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ትዕግሥት ፍስሀ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ አዲስ የከተማ ልማት ምዕራፍ ውስጥ እየገባች ሲሆን፥ ትኩረቱም ከተሞችን ማሰፋፋት ላይ ብቻ ሳይሆን ምርታማነታቸውን ማሳደግ እንዲሁም ምቹ፣ ተወዳዳሪ፣ ሁሉን አቀፍና ዘመናዊ ከተሞች ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለጋራ ብልፅግና ቀጣይ ሞተር እንዲሆኑ ማድረግ ነው።