የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

“የተመራጩ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌን የበዓለ ሲመት ሥነ-ሥርዓት ለመታደም ዛሬ ጅቡቲ ተገኝቻለሁ።‎‎ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ለሃገራቸው የሚሰጡት አገልግሎት ሁለንተናዊ እድገትን እንዲያስቀጥል ‎ልባዊ ደስታዬንና መልካም ምኞቴን ልገልጽ እወዳለሁ። በኢትዮጵያ እና በጅቡቲ መካከል ያለው የቆየ ወዳጅነት እና ስትራቴጂካዊ አጋርነት ለሕዝቦቻችን የጋራ ብልጽግና እንዲሁም ለቀጣናችን ሰላምና መረጋጋት መጠናከር መሰረት እንዲሆን እመኛለሁ።” ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮችhttps://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለተመራጩ የጅቡቲ ፕሬዝደንት ኢስማኢል ኦማር ጊሌ የበዓለ ሲመት ሥነ-ሥርዓት ለመታደም ጅቡቲ ገብተዋል።

#PMOEthiopia ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication See less

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

‎”የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀውና ባለፉት ዓመታት በሚዲያ ዘርፍና ተቋማት ላይ የተመዘገቡ ስኬቶች በቀረቡበት የምክክር መድረክ ላይ ታድሜ ሀሳቤን አጋርቻለሁ።‎‎ባለፉት ስምንት ዓመታት የሚዲያ ምህዳሩን በዲሞክራሲያዊ አውድ ለመዋጀት በወሰድነው እርምጃ ለሀገር ግንባታ የሚረዳ መሠረት ጥሏል። ይህ ውጤት እንዲቀጥልም ሚዲያዎች ከዋልታ ረገጥነትና ከጽንፈኝነት ወጥተው በእውነት ላይ የተመሠረተ ትርክት በመገንባት፣ ለጋራ ማንነትና ለብሔራዊ መግባባት በቁርጠኝነት…

በኢትዮጵያ የዘመናዊ ሚዲያ ታሪክ ፈር ቀዳጁና የጥንቱ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን

ቢኒያም ኤሮ ፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ በኢትዮጵያ የዘመናዊ ሚዲያ ታሪክ ፈር ቀዳጁና የጥንቱ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን፣ የነበሩበትን ዘርፈ ብዙ ተግዳሮቶች ለመፍታት የለውጡ መንግሥት በዘርፉ ያደረገው ሪፎርም ተቋሙ ዓበይት የለውጥ እመርታዎችን እንዲያሳይ በር ከፋች ነበር ሲሉ አካፍለዋል። መዋቅራዊ ክፍተቶች፣ ግልጽ ያልሆነ ኤዲቶርያል ፖሊሲ፣ የብዝሃነትና ተደራሽነት ፈተና እንዲሁም የቴክኖሎጂ ኋላ ቀርነት ተቋሙን የፈተኑት ማነቆዎች…

የኢትዮጵያ የህትመት ዘርፍ የለውጡ መንግሥት ትልቅ ትኩረት በመስጠት ሰፊ ሪፎርም ካደረገባቸው ዘርፎች አንዱ ነው።

መሳፍንት ተፈራ፣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ እንደገለጹት የኢትዮጵያ የህትመት ዘርፍ የለውጡ መንግሥት ትልቅ ትኩረት በመስጠት ሰፊ ሪፎርም ካደረገባቸው ዘርፎች አንዱ ነው። ‎በተለይም የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ያጋጠመውን ተቋማዊ ውስንነቶች በመለየት ተገቢውን ምላሽ መስጠት የሪፎርሙ ተቀዳሚ እርምጃ ነበር። የይዘት ጥራትና ብዝሀነትን ማስፋት፣ ሚዲያውን በቴክኖሎጂ ማዘመን፣ ተደራሽነትና ስርጭትን ማሳደግ እንዲሁም ተገቢ አደረጃጀትና መዋቅር መፍጠር የሪፎርሙ ትግበራዎች…

ከለውጡ በፊት የሚዲያ ተቋማት ዘርፈ ብዙ ስብራቶች ነበሩባቸው፤

ሀይማኖት ዘለቀ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር እንደተናገሩት ከለውጡ በፊት የሚዲያ ተቋማት ዘርፈ ብዙ ስብራቶች ነበሩባቸው፤ ከነዚህም ጥቂቶቹ የፖሊሲ እና የማዕቀፍ ፣ የመዋቅር አደረጃጀት፣ ተቋማዊና የትክክለኛ ሙያዊ ስነ-ምግባር ስብራቶች ይገኙበታል። ‎የለውጡ መንግስት እንዚህን ስብራቶች ለማከም ጥልቅ የሆነ የሚዲያ ሪፎርሞችን አድርጓል። ሪፎርሙ ካሳካቸው ለውጦች መካከል፤ ተጠሪነቱ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሆነ የመገናኛ ብዙሃን ባልስልጣን ማቋቋም፣…

አሁን በመካሄድ ላይ!

‎‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት “የሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ” በሚል መሪ ቃል ሀገራዊ የምክክር መድረክ መካሄድ ጀምሯል።‎ኢትዮጵያ ካስመዘገበቻቸው የለውጥ ድሎች አንዱ ተቋማት ጠንካራና ትክክለኛ የዴሞክራሲ ስርዓት መገለጫ እንዲሆኑ ማድረግ ሲሆን፣ ከነዚህም መካከል የመገናኛ ብዙሃን ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ናቸው። ‎

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

“ከኔዘርላንድስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሮብ ጄተን ጋር ውጤታማ የሥልክ ውይይት አድርገናል።‎በውይይታችን የሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ የመከርን ሲሆን፣ በተለያዩ ዘርፎች ያለንን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚያስችሉ መንገዶች ላይ ሃሳብ ተለዋውጠዋል።” ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮችhttps://linktr.ee/FDREGovermentCommunication