ኢትዮጵያ ለአፍሪካውያን የምታቀርባቸው በርካታ ተሞክሮዎች አሏት

“የውሃ ዋስትና ለአፍሪካ ብልጽግና፤ የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ መሪ ቃል” ኢትዮጵያ ከየካቲት 6 እስከ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የአፍሪካ-ጣሊያን ጉባኤን እና 39ኛውን የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤን በደመቀ ሁኔታ እንደምታስተናግድ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ የዘንድሮው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ “የ2063 አጀንዳን ለማሳካት ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና የንፅህና አጠባበቅን ማረጋገጥ”…

የአፍሪካ-ጣሊያን ጉባኤ በአፍሪካ አፈር ሲካሄድ የመጀመሪያ መዳረሻውን ኢትዮጵያ አድርጓል

የአፍሪካ-ጣሊያን ጉባኤ በኢትዮጵያ መካሄዱ የአፍሪካ-ጣሊያን ግንኙነት በአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የትብብር ማዕቀፎች ይበልጥ እንዲጠናከር የሚያደርግ መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ። የአፍሪካ-ጣሊያን ፎረም መካሄድ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ከሮም ውጭ ሲካሄድ ይህ የመጀመሪያው ነው ያሉት የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ፣ በአፍሪካ አፈር ሲካሄድ የመጀመሪያዋ መዳረሻ ኢትዮጵያ መሆኗ ሀገራችን አፍሪካን ከተቀረው ዓለም ጋር ከማስተሳሰር አንጻር ያላትን…

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

“ዛሬ የሳዑዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዑል ፋይሰል ቢን ፋርሃን አል ሳዑድን ተቀብዬ በሁለትዮሽ እና ባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት አድርገናል። ‎ውይይታችን በዐበይት ዘርፎች ለረዥም ዘመናት የዘለቀውን የሁለቱ ሀገሮቻችንን ትስስር በማስፋት እና የወል ፍላጎቶቻችን በሆኑ ቀጣናዊ እና አለምአቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ትብብራችንን በማጠናከር ላይ ያተኮረ ነበር።” ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

“ኢትዮጵያ 39ኛውን የአፍሪካ ህብረት እና 2ኛውን የጣልያን-አፍሪካ ጉባዔዎች የሚካፈሉ ከፍተኛ ልዑካንን ለመቀበል ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ ሆናለች። በከፍተኛ ጥራትና ዘመናዊ መልክ የተገነቡት ዓለም አቀፍ የስብሰባ አዳራሾች እና ደረጃቸውን የጠበቁ ምቹ እና ዘመናዊ የቱሪዝም መዳረሻዎች በታጀበው አዲሱ ገጽታችን፤ ቆይታዎ ከምንጊዜውም በላይ ልዩ እንደሚሆን እናረጋግጥሎታለን፡፡ ከጉባዔ አዳራሾች ባሻገር በአፍሪካውያን የሚመራውን አዲሱን የቱሪዝም ዘርፍ እድገት፣ ተሳታፊዎች እንዲመለከቱና ቆይታቸውን…

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የሰው አልባ ፖሊስ አገልግሎት ያስጀመሩበት ሥነ ስርዓት

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የሰው አልባ ፖሊስ አገልግሎት ያስጀመሩበት ሥነ ስርዓት

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/FDREGovermentCommunication

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

ውድ ኢትዮጵያዊያን በዚህ ሳምንት ውዷ ሀገራችን በአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ለመታደም የሚመጡ እህት ወንድም አፍሪካዊያንን ለመቀበል ልቧን ከፍታ-እጆቿን ዘርግታ ትቀበላለች። እነዚህ ወዳጆቻችን የሰንደቃችንን ቀለማት የሚጋሩ፣ ኢትዮጵያን እንደነፃነት ቀንዲል የሚመለከቱ ብሎም ሀገራችን የአኅጉሩ የፖለቲካ ርዕይ የማዕዘን ድንጋይ አድርገው የሚያከብሩ ናቸው። ኢትዮጵያ ወደር በሌለው እንግዳ ተቀባይነቱ ለምን ልትከበር እንደበቃች በአቀባበላችን እናሳያቸው። እንደቤታቸው እንዲሰማቸው እናድርግ። በክብር እንቀበላቸው። በፍቅር እናቆያቸው።…

የሰርቪስ ሴክተር አፈጻጸምን በተመለከተ፣

• የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመት 8 ሚሊዮን ሰዉ ሲያጓጓዝ የነበረ ሲሆን፣ ባለፉት 6 ወራት 10.7 ሚሊዮን ሰዉ አጓጉዟል፡፡ በዚህ ዓመት በትንሹ ወደ 22 ሚሊዮን ለማድረስ እየተሰራ ነዉ፡፡ አየር መንገዱ በመጠን፣ በመዳረሻና በሚያጓጉዘዉ ሰዉ በእጅጉ ጨምሯል፡፡ • ሞባይልን በተመለከተ በለዉጡ ጊዜ 37 ሚሊዮን ዜጎች ሞባይልን ይጠቀሙ ነበር፡፡ ዘሬ ኢትዮ-ቴሌኮም ብቻ 87 ሚሊዮን ዜጎች፣ ሳፋሪኮም ደግሞ ከ10…

ኢኮኖሚ ጉዳዮችን በሚመለከት

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክ ሪፎርም ከያዛቸው ዋነኛ ዓላማዎች መካከል አንደኛው የማክሮ ኢኮኖሚ ስብራትን ማረጋጋት ነው። ሁለተኛው የኢኮኖሚ አቅጣጫዎችን ከግብርና መር ወደ ብዝሃ ዘርፍና ብዝሃ ተዋናይ በማሸጋገር ጥራት ያላው እድገት ማስመዝገብ ሲሆን ሌላኛው የኢትዮጵያን የእዳ ጫና ማቃለል ነው። በዚህ ረገድ በሁሉም መመዘኛ በኢትዮጵያ አመርቂ የኢኮኖሚ ስኬት ተመዝግቧል። #የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia