የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
“ዛሬ ምሽት ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጆርጅ ኤሎምቢ እና ከባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ጋር በአጋርነት፣ ዕድገት እና በአፍሪካ የወደፊት ዕድሎች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።”
“ዛሬ ምሽት ከአፍሪ ኤክሲም ባንክ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጆርጅ ኤሎምቢ እና ከባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ጋር በአጋርነት፣ ዕድገት እና በአፍሪካ የወደፊት ዕድሎች ዙሪያ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።”
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
“የአውሮፓ ሕብረት የውጭ ጉዳይና የደህንነት ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይ የተከበሩ ካያ ካላስን ዛሬ ተቀብዬ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል። በአውሮፓ ሕብረት እና በአፍሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ማጠናከር ላይ የመከርን ሲሆን በጋራ ጥቅሞች እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሃሳብ ተለዋውጠናል።በተጨማሪም ትኩረት የሚሹና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መሰረት ባደረገው ውይይታችን፤ ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ይበልጥ ለማሳደግና ለማስፋፋት በሚያስችሉ መንገዶች ላይ መክረናል።”…
“በዚህ ታሪካዊ ሀገራዊ ምክክር የማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ለመታደም በመታደሌ ታላቅ ኩራት ይሰማኛል። በሚቀጥሉት ሳምንታት አራት ሺህ ተሳታፊዎችን በአንድ ጣሪያ ስር የሚያሰባስበው ይህ ታላቅ ጉባኤ፣ ኢትዮጵያ በገዛ እጇ አዲስ ታሪክ ለመጻፍ የሚያስችላትን “ብዕርና ብራና” ያገኘችበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዞ በኃይለ ቃል ጀምሮ በኃይለ እርምጃ የሚደመደምበትን አዙሪት ሰብረን በንግግርና በውይይት የምንተካበት ወቅት ላይ እንገኛለን። ለዚህ…
የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት እና የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልክተኛ ክቡር ቺፍ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ በሀገራዊ ምክክር ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያን ታሪክ፣ የህዝቦቿን ብዝሃነትና ታታሪነት በመጥቀስ ይህ ህዝብ የሰነቀውን ብሩህ ተስፋ ለማሳካት ደግሞ አሁን የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ስኬት ቁልፍ መሆኑን አብራርተዋል። PMOEthiopia ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮችhttps://linktr.ee/FDREGovermentCommunication
ባስተላለፉት መልዕክት፤ በዓለም ታሪክ ውስጥ በግጭት የተገነባ ወይም ያተረፈ ሀገር አለመኖሩን አስገንዝበዋል። አክለውም በፖለቲካ ባህል ውስጥ ልዩነቶች መኖራቸው ተፈጥሮአዊ ቢሆንም፤ ትልቁና መሰረታዊው ስህተት ግን እነዚህን ልዩነቶች በኃይል ለመፍታት መሞከር እንደሆነ ነው ያነሱት። ከሁሉ በላይ ልዩነቶችን መፍታት የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ፣ በመነጋገርና በተለያዩ ሰላማዊ መድረኮች መሆኑን ያብራሩት ዋና ፀሐፊው፤ ኢትዮጵያም ለዚህ የሚሆኑ በርካታ ባህላዊ የምክክር መንገዶች ያሏት…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አመራሮች ጋር በመሆን፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑን የአራት ዓመታት ጉዞ የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ጎብኝተዋል። #PMOEthiopia
ይህ አዲስና ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ለአሁኑም ሆነ ለሚመጣው ትውልድ የምስራች ነው። ኢትዮጵያ በጦርነት የተመሰረተች ሀገር ሳትሆን በሕዝቧ መግባባት እና በጋራ ትርክት ላይ የምትገነባ መሆኗን የሚያረጋግጥ ወሳኝ የሀገር ግንባታ ሂደት ጭምር ነው።
“ዛሬ በታሪካዊው የሀገራዊ ምክክራችን ዋዜማ፣ የኢትዮጵያ ታላቅ ወዳጅ የሆኑትን ክቡር ኦሊሴጉን ኦባሳንጆን በጽሕፈት ቤቴ ተቀብያለሁ። በመጪው ሀገራዊ ምክክር ዙሪያ ለመወያየት እንዲሁም ከዚህ ቀደም ካከናወኗቸው ተግባራት ጥበብ ለመቅሰም ችለናል፤ በተለይም የቢያፍራን የሰላም ሂደት በመምራት ያካበቱትን ልምድ አጋርተውናል። ይህም ኢትዮጵያ በምክክር ለምታረጋግጠው አንድነትና ዘላቂ የሰላም ጉዞ ላይ ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ ነው። ኢትዮጵያ ለምታበረክቱት በዋጋ የማይተመን አስተዋጽኦ ሁልጊዜም…